ምዕመናን በድንኳንና ዉሥጥ
ዕመናን በድንኳንና ዉሥጥ
                                            

               


                                                   15ኛሐዊረ ሕይወት/የሕይወት ጉዞ/ 2011



ነገረ ክርስቶስ በተዋሕዶ ክፍል አንድ

 Image may contain: 11 people      

ጉባኤ ኒቅያ
በቤተክርስትያን ታሪክ ከተነሱ መናፍቃን ሁሉ እንደ አርዮስ የከፋ የለም::
ኅዳር 9-እጅግ የከበሩ ሃይማኖታቸው የቀና 318ቱ ቅዱሳን አበው ሊቃውንት በ325 ዓ.ም በኒቅያ አርዮስን ያወገዙበት ዕለት ነው፡፡
አርዮስ መሠረታዊ ትምህርቱን በሊብያ ካጠናቀቀ በኋላ ወደ እስክንድርያ በመጓዝ በእስክንድርያ ከፍተኛ ት/ቤት ትምህርት አጠናቆ እንደጨረሰ ወደ መካከለኛው ምሥራቅ ሄዶ በአንጾኪያ ከፍተኛ መንፈሳዊ ት/ቤት ገብቶ የትርጓሜ መጻሕፍትና የነገረ መለኮት ትምህርት ተምሯል፡፡ በጊዜውም ሉቅያኖስ ከተባለ መናፍቅ ዘንድ ተምሯል፡፡ አርዮስ አብዛኛውን የኑፋቄ ትምህርት ያገኘው ከሉቅያኖስና በአንጾኪያ ት/ቤት ከሚገኙ ሌሎች መናፍቃን ነው፡፡ በአንጾኪያ ትምህርቱን ከጨረሰ በኋላ ወደ እስክንድርያ ተመልሶ ኑሮውን በዚያው አደረገ፡፡
እነዚህም እጅግ የከበሩ ቅዱሳን መጀመሪያ አርዮስን አስተምረው ለመመለስ መጀመሪያ በኒቅያ የተሰበሰቡት መስከረም 21 ቀን ነው፡፡ ከሃዲው አርዮስ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስን ‹‹ወልድ ፍጡር ነው›› ብሎ በመነሣቱ ቤተ ክርስቲያን ለብዙ ዓመታት እንድትታወክና እንድትበጠበጥ ምክንያት ሆኗል፡፡
ከመስከረም 21 እስከ ሚያዝያ 21 ተጠቃለው ኒቅያ ገቡ:: በ325 ዓ/ም ለ40 ቀናት የሚቆይ ሱባኤን ያዙ:: ሱባኤውን ሲጨርሱም በ4ቱ ፓትርያርኮች (እለእስክንድሮስ: ሶል ጴጥሮስ: ዮናክንዲኖስና ኤዎስጣቴዎስ) መሪነት: በእለእስክንድሮስ ሊቀ መንበርነት: በአትናቴዎስ ጸሐፊነት ጉባኤው ተጀመረ::
በጉባዔው ላይ ከተገኙት አባቶች መካከል ቅዱስ ቶማስ ዘመርዓስ : ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ቅዱስ እለእስክንድሮስ ሊቅ ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስ እና ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘአርማንያ ይገኙበታል::
በጉባኤው ሙሉ ስልጣን በሰማይ ከፈጣሪ: በምድር ከንጉሡ የተሰጣቸው አበው አርዮስን ተከራክረው ከነ ጀሌዎቹ ምላሽ አሳጡት:: ክርስቶስ አምላክ ወልደ አምላክ: ሥግው ቃል: ራሱም እግዚአብሔር መሆኑን አስረዱት::
በጉባኤው መጨረሻም አበው ሊቃውንት 318ቱ በአንዲትም ቃል ሆነው ዛሬ ላይ የጸሎታችን መጀመሪያ የሆነውን ‹‹ጸሎተ ሃይማኖትን›› ደነገጉልን ሃይማኖትን አጸኑልን፡፡
የከበረች በረከታቸው ድል የማትነሣ ረድኤታቸው ጥርጥር የሌለባት ሃይማኖታቸው ከእኛ ጋር ትሁን ሥሉስ ቅዱስን ያለማጉደል ያለ መጨመር እናምናለንና ክፉዎች ሰዎች ከመከሩት ምክር ከሰይጣን ጠላትነት ታድነን ለዘለዓለሙ አሜን፡፡
መልካም ሰንበት

በትዳር ሕይወት የወላጆች ኃላፊነት


                                                                  ዲ/ን ተመስገን ዘገየ
መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር አምላክ ሰውን በአርአያውና በአምሳሉ ፈጠረው ይለናል (ዘፍ፪-፳፮) አዳም ብቻውን ይሆን ዘንድ ያልፈቀደውና ብቻውን ቢሆን መልካም እንዳልሆነ የሚያውቅ አምላካችን የምትረዳውን ሔዋንን ከጎኑ አጥነት ፈጥሮለታል፡፡እግዚአብሔር ወንድና ሴት አድርጎ መፍጠሩ ለበረከት፤ለመባዛት በመሆኑ”ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሉአት” በማለት ሕገ በረከትን ሰጥቷአቸዋል፡፡ስለዚህ ጋብቻ በሰው ፍላጎት ብቻ የተገኘ አይደለም፡፡ስለ ጋብቻ በኦሪትም በወንጌልም ሕግ ተሰርቷል፡፡የአዳምና የሔዋን ጋብቻ የሕጋዊ ጋብቻ መሠረት ነው፡፡ጋብቻን ያከበሩ በሕጋዊ ጋብቻ የነበሩ ደጋግ ቅዱሳን በሕገ ልቡና እንደነበሩ ሁሉ በሕገ ኦሪትም ነበሩ፡፡ለምሳሌ የኢያቄምና የሐና ጋብቻ ቅዱስ ጋበቻ ነበር፡፡የተቀደሰ ጋብቻ በመሆኑ የቅድስት ድንግል ማርያም ወላጆች የአምላካችን የመድኀኒታችን አያቶች ለመሆን በቅተዋል፡፡
እንዲሁም የዘካርያስና የኤልሣቤጥ ጋብቻ የተባረከ ጋብቻ ነበር፡፡ ቡሩክና ሕጋዊ በመሆኑም መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስን ማግኘት ችለዋል፡፡ጋብቻ የቅድስና ሕይወትን በሥርዓት የሚመሩበት የቤተሰብ መንግሥት በመሆኑ ክብሩና ልዕልናው ሊጠበቅ ይገባዋል፡፡ወላጆች ልጆችን መተካት አለባቸው ሲባል“መውለድ” ብቻ ማለት አለመሆኑን በሚገባ መረዳት ይገባል፡፡ቅዱስ ዳዊትም “ናሁ ጸጋሁ ለእግዚአብሔር ውሉድ ዕሤተ ፍሬሃ ለከርሥ፤ልጆች የእግዚአብሔር ስጦታ ናቸው (መዝ፻፳፮፥፫) ልጆች ማደግ ያለባቸው በእግዚአብሔር ትእዛዝና መንገድ ነው፡፡ክቡር የሆነው የሰው ልጅ ቀርቶ አራዊትም እንኳን ልጆቻቻውን በሥርዓት ያሳድጋሉ፡፡ ለምሳሌ፤አናብስትና አናብርት አዳኝ የዱር እንሰሳት ልጆቻቻውን እንዴት እያደኑ ማደግ እንዳለባቸው ያስተምራሉ፡፡
ጠቢቡ ሲራክ “የሰው አነዋወሩ በልጆቹ ይታወቃል”ይላል (ሲራ፲፩፥፳፰) በ፳፩ኛው ክፍለ ዘመን የወጣቱ ሥነ-ምግባር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየዘቀጠ መምጣቱ እውነት ነው፡፡ለዚህም ዋናው መሠረታዊ ችግር ሕዝቡ ከእግዚአብሔር ጋር ያለው ግንኙነት በተለያየ ምክንያት እየዛለ መምጣ ነው፡፡ወላጆች ልጆቻቸውን ማስተማር ያላባቸው ቀዳሚ ትምህርት“እግዚአብሔርን መፍራት“ነው፡፡(ምሳ፩፥፯) ልጆች ለሚጠይቁት ጥያቄ እንደ ዐቅማቸው ማስረዳት ይገባል፡፡ ሕፃናትን የሚያስተምሩ ሰዎች በፍቅርና በደስታ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ልጆች ከጣፈጭ ምግብ ይልቅ የሚረኩት ከወላጆች በሚያገኙት ፍቅር ነው፡፡ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “አባቶች ሆይ ልባቸው እንዳይዝል ልጆቻችሁን አታበሳጩ”ይላል (ቈላ፫፥፳፪) ልጆችን በፍቅር እንጂ በስድብ ፤በመደብደብ ፤በማበሳጨት፤በማስፈራራት ለማስተማር መሞከር እንደማይገባን ሐዋርያው አስተምሮናል፡፡
ሲራክ“የሰው አኗኗሩ በልጆቹ ይታወቃል (ሲራ፲፩፥፳፰) የላኪው ማንነት በተላከው እንደ ሚታወቅ የወላጆች ምንነት ማሳያ ልጆች ናቸው፡፡የኢትዮጵያ ሕዝብ ሥነ ምግባር የማይታይበት ልጅ ሲያጋጥማቸው”አሳዳጊ የበደለው” ይላሉ፡፡ስለዚህ ልጆችን በሥነ ምግባር ኮትኩቶ ማሳደግ ለነገ የማይባል ተግባር ነው፡፡አሁን አሁን በልጆቹ የሚደሰትና የሚጠቀም ወላጅ ሳይሆን በወለዷቸው ልጆች የሚያዝኑና የሚያለቅሱ ኢትዮጵያውያን ይበዛሉ፡፡ሲራክ “በሱ ጥፋት አንተ እንዳታፍር ልጅህን አስተምረው ያገለግልሃል”(ሲራ፴፥፲፫) ልጅን በሚገባ አስተምሮ ማሳደግ በጣም አስፈላጊ መሆኑን ቅዱሳት መጻሕፍት ያሰተምሩናል፡፡ የካህኑ የዔሊ ልጆች ፊንሐስና አፍኒን በታቦተ ጽዮን ድንኳን ሥር ያመነዝሩ ነበር ያሳፍራል፡፡ ዔሊ ልጆቹ ይህን የመሰለ ኃጢአት መፈጸማቸውን እያወቀ ባለመገሰጹ ቅጣት ተቀብሏል፡፡ልዑል እግዚአብሔር ዔሊን “ከእኔ ይልቅ ልጆችህን ለምን አከበርክ?(፩ኛሳሙ፪፥፳፱) በማለት ተቆጣው፡፡ሁለት ልጆቹንም ቀሰፋቸው፡፡ቅጣቱ በልጆቹና በእሱ ብቻ ተወስኖ አልቀረም፡፡ለሌላም ተረፈ አንጂ፡፡
ወላጆች ሆይ ልጆቻችንን እንዴት እናሳድጋቸው?
የነገው ትወልድ ሀገሩንና ቤተሰቡን የሚጠቅም በሥነ- ምግባር የታነጸ በሥራው የተመሰገነ ይሆን ዘንድ ዛሬ ያሉትን ልጆች በአግባቡ መያዝ ልዩ እንክብካቤ ማድረግ ይገባል፡፡ወላጆች ከማንም በላይ ሕፃናትን መልካሙንና ክፉንም በማሰተማር ቅርብ ናቸው፡፡እናትና አባት ከትምህርት ቤት ሲመለሱ ስለተማሩት ትምህርት መጠየቅ አለባቸው፡፡ልጆችም እንደሚጠየቁ ስለሚያውቁ ትኩረት ሰጥተው ይከታተላሉ፡፡ጥሩ ነገር በሠሩ ጊዜ ጥሩ ወጤት ባመጡ ጊዜ ሽልማት ማዘጋጀት ይገባል፡፡ወላጆች በቤት ውስጥ በቃል ሳይሆን በተግባር በክፉነት ሳይሆን በደግነት እያስተማሩ ሊያሳድጉ ይገባል፡እንዲህ ከሆነ የክፉ ምግባር ቦይ አይሆኑም፡፡አንድ ሰው በቅሎ ጠፋችበትና ወዲያ ወዲህ እየተንከራተተ ሲፈለግ በበቅሎ ሌብነት የሚጠረጠረው ሰው አብሮ ያፋልገው ጀመር፡፡ዘመድ መጥቶ “በቅሎህ ተገኘችልህ ወይ”ብሎ ቢጠይቀው አፈላላጊዬ የበቅሎዬ ሌባ ስለሆነ እንደምን አድርጌ በቅሎዬን ላገኛት እችላለሁ አለ ይባላል፡የልጆችን አእምሮዊ ዕድገት ለማሟላት ከሚደረጉ እንክብካቤዎች የሚከተሉት ይጠቀሳሉ
ተገጣጣሚ መጫዎቻዎችን በመጠቀም የቁጥር ስሌት እንዲያውቁ ማድረግ፤የቋንቋ ችሎታቸውን የሚያሳድጉ መንፈሳዊ ጹሑፎችን እንዲያነቡ ደጋግመው መንገርና ዕድሎችን ማመቻችት፡፡ወላጆች (ባልና ሚስቱ) በአንድነት ሁነው የቤተሰቡ መሪ በመሆናቸው ሊወስዱት የሚገባ ተግባር ይኖራል፡፡ልጆቻችንን በምግባር በማሳደግ የሚኖሩበትን ቤት የዕለት ከዕለት እንቅሰቃሴ እየተከታተሉ መሥመር በማስያዝ አገልጋዮች የሆኑ የቤት ሠራተኞችን ሳያማርሩ ሥራ ሳያበዙ በማሠራት መኖር ይጠበቅባቸዋል፡፡ወላጆች ይህንን ከባድ የቤተሰብ ኃላፊነት ሲወጡ በሚከተሉት ነጥቦች ቢመሩ መልካም ነው፡፡
፩.. በፍቅር፤ ልጆች ፍቅርን እንክብካቤን ከወላጆችና ከመምህራን ይፈልጋሉ፡፡የወላጆቹን ፍቅር እያገኘ ያደገ ልጅ መንፈሰ ጠንካራ፤ለሰው የሚያዝንና ታዛዥ ይሆናል፡፡አንዳንድ ወላጆች የቤተሰቡ ራስ መሆናቸውን በቊጣ በዱላ በመግለጽ ልጆቻቸውን በኃይል ብቻ ለመግዛት የሚሞክሩ አሉ ፡፡ይህ የተሳሳተ መንገድ ነውና ከስሕተት ጎዳና መመለስ ይኖርባቸዋል፡፡
፪..ትኩረት በመስጠት፣ ልጆች ከፍተኛ የሆነ ክትትልና ትኩረት ይፈልጋሉ፡፡የሚያከናውኑትን እያንዳንዱን ተግባራት እየተመለከተ በጎውን በጎ የሚላቸው ሲሳሳቱ የሚያርማቸው ይሻሉ፡፡ ልጆችን በንቃት መከታተል የወላጆችና የመምህራን ግዴታ ነው፡፡ወላጆች በዕረፍት ጊዜ ከልጆቻቸው ጋር መወያየት፣መመካከር፣የወደፊት ዕቅዳቸውን ምኞታቸውን በተመለከተ በግልጽነት መረዳት ይገባቸዋል፡፡
፫. በማስተማር፤ ንግሥት ዕሌኒ ቆስጠንጢኖስን በሥርዓት ኮትኩታ በማሳደጓ የሀገረ መሪ ለመሆን በቃ፡፡አሁንስ እኛ ልጆቻችንን እንዴት እያሳደግናቸው ነው? ሰው በሕፃንነቱ ተክል ማለት ነው፡፡ተክል የሚሆነውን ሁሉ ሊሆን ይችላል፡፡ቀጥ ብሎ ያድጋል ተወላግዶም ያድጋል የተወላገደውን ለማቃናት ብዙ ዋጋ ያስክፍላል፡፡ወላጆች በልጆቻቸው ዕድገት ትኩረት ሊሰጡት የሚገባ አንዱና ዋነኛው የልጆቻቸውን ተፈጥሮዊ ተሰጥኦ ማበልጸግ ነው፡፡ወላጆች ልጆችን የማሳደግ ክህሎት ለማዳበር ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ ይኖርብናል፡፡ከእኛ ቤት ሲገባ ግን መጸሕፍት ይኖር ይሆን? በተለያዩ የቤተሰብና የልጆች ነክ ጉደዮች በመሳተፍ ከተቻለ የሥነ ልቡና ባለሙያና የአብነት መምህራንን በማማከር የተሻለ ዕውቀት መጨመር ይቻላል፡፡
የልጆችን ተሰጥኦ ከልጅነታቸው ጀምሮ መረዳትና እውቅና መስጠት ለወላጆች ትልቅ ስኬትና አበረታች ነገር ነው፡፡ወላጆችና የአብነት መምህራን ልጆች ችሎታቸውን የሚያወጡበትን አማራጮችና ዕድሎችን ማመቻችት ይገባቸዋል፡፡በእኛ ሀገር ደረጃ ጥረህ ለፍተህ ብላ ኑር ነው እንጂ አማራጭ አንሰጥም ይህ ዘመንን አለመዋጀት ነውና መስተካከል ይኖርብናል፡፡የልጆችን እንቅስቃሴ በመከታተል የልጆችን ፍላጎት ማወቅ ይገባል፡፡ወላጆች ከትምህርት ስኬት ባሻገር የልጆቻቸውን ማኀበራዊ መንፈሳዊና ሥነ-ልቦናዊ ሕይወት መረዳት አለባቸው፡፡ወላጆችና መምሀራን ልጆችን ሲያናግሩ ሙሉ ትኩረት መስጠት አለባቸው፡፡
ልጆችን በልዩ ልዩ እንቅስቃሴዎች ማሳተፍ ይገባል
ወላጆች ልጆቻቸውን ሲያሳድጉ በትምህርታቸው ብቻ ስኬታማ ሆነው ትምህርታቸውን አጠናቀው እንዲመረቁ ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ በመንፈሳዊ ሕይወታቸውም ስኬታማነት እንዲ ዘጋጁ የማደረግ ኃላፊነት አለባቸው፡፡ልጆችን ከትምህርት ቤት መልስ በተለያዩ ተግባራት እንዲሳተፉ ማድረግ የሚከተሉት ጠቀሜታዎች ይኖሩታል፡፡
ቴሌቪዥን በመመልከትና ጌም በመጫዎት የሚያሳልፉትን ጊዜ በመገደብ በሠርክ ጉባኤና በሰንበት ትምህርት ቤት ከመደበኛው ከትምህርት ውጭ የሆኑ ተግባራት ሲሳተፉ ወሳኝና ለወደፊት ሕይወታቸው ከፍተኛ ጠቀሜታ ያላቸው ማኀበራዊ ክህሎቶችን እንዲያዳብሩ ይረዳቸዋል፡፡ በውኃ ውስጥ መዋኘትም ለልጆች የሚመች የእንቅስቃሴ አይነት ነው፡፡በሳምንት ሁለት ጊዜ (ቅዳሜና እሑድ) ቢዋኙ አካላዊ ብቃታቸውን ያሻሽላል፡፡የመተንፈስ እንቅስቃሴ በማሻሻል ሂደት ለልጆች ጤንነት የአካል ብቃት የላቀ አስተዋጽኦ አለው፡፡ከትምህርት ቤት መልስም ሆነ በዕረፍት ቀናት የእግር ኳስ እንቅስቃሴ ማድረግ ወላጆች አብረው በመጫወት ካልተቻለም ልጆች ሲጫወቱ በመከታተል ,.በተግባር በማሳየት፣ልጆች ከሚሰሙት ይልቅ በሚያዩት ይሸነፋሉ፡፡ ከተነገራቸው ይልቅ የተመለከቱት በእነርሱ ኀሊና ትልቅ ቦታ አለው፡፡ ወላጆች ተግባራዊ የሆነ ሕይወትን ለልጆቻቸው ሊያስተምሩ ይገባል፡፡አሁን በየቤታችሁ ልጆች ምንድን ነው የሚያዩት አንዳንድ ወላጆች ልጆቻቸውን እንዳይጠጡ እየመከሩ እነርሱ ጠጥተው የሚገቡ አሉ፡፡አሁን የዚህ ሰውየ ልጅ ምን ይሆናል? ልቡ ባዶ ቅርጫት ራሱ ባዶ ቤት እየሆነ ነው፡፡ ፈቃደ ሥጋን ለፈቃደ ነፍስ በማስገዛት ልጆችን መልካም የሆኑ ነገሮችን ማስተማር አለብን አንድ ወቅት ሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ “ራሱን ያሸነፈ የጎበዝ ጎበዝ ነው ሌለውን ያሸነፈ ተራ ጎበዝ ነው” ብለው ነበር፡፡ በዘመናችን ራስን ማሸነፍ ሰማዕትነት ነው፡፡
• ልጆች ማኅበራዊ ሚዲያዎችን በአግባቡ መጠቀም ይኖርባቸዋል
የመረጃ ልውውጥ ከማደረግ (በጎን መጥፎውንም) ማኅበራዊ ግንኙት ከማጠናከር (የጠፉ ጓደኞችን) ከማገናኘት አንጻር በአግባቡ ከተጠቀሙበት ትልቅ አስተዋጽዖ አለው፡፡የማኅበራዊ ሚዲያዎች ጉዳት ተመልሶ የማይገኝ ጊዜን ያባክናል፡፡አጠቃቀማችን በአግባቡ ካልሆነ ለትዳር ጠንቅ ነው ራሳቸውን አግዝፎ ለማሳየትና ማኅበራዊ ሚዲያዎችን ለዝሙት የሚጠቀሙ አሉ፡፡ በዘመናችን ችግሩን መናገር በራሱ ችግር ነው እንጂ ቴክኖሎጂው እየተራቀቀ ሲመጣ የትውልዱም ጥያቄ እንዲሁ እየተበራከተ ይመጣል፡፡የ፳፩ኛውን ክ/ዘመን ትውልድ ሥነ ልቡና በመረዳት ወላጆች እንደ እባብ ብልህ በመሆን ትውልዱ ያለበትን ሁኔታ ቀድመው ምን እየመጣ እንደሆነ መመልከት ይኖርባቸዋል፡፡
የመረጃ ቴክኖሎጂ ዓለምን ወደ አንድ መንድር እየተቀረ በመምጣቱ ሀገራችንም የዚሁ ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ በመሆኑ አደጋ አለው፤በአግባቡ መጠቀምና መቆጣጠር አለመቻል መሠረታዊ ችግር ነው፡፡ልጆቻችን ውጤታማና ስኬታማ እንዲሆኑ ለማድረግ የመረጃ ቴክኖሎጂ አጠቃቀማቸውን መገደብና መቆጣጠር የወላጆች ኃላፊነት ነው፡፡ልጆች በቪዲዮ ጌም መጫወት ካለባቸው በወላጆች በጥንቃቄ የተመረጡ፣አዝናኝና የልጆችን የፈጠራ ችሎታ የሚያበለጽጉ ፣ለዕድሜአቸውና ለሥነ-ልቡናቸው የሚመጥኑ ቁጣና ጥቃት ያልበዛባቸው መሆን እንዳለባቸው ባላሙያዎች አበክረው ይመክራሉ፡፡የሚያስፈሩ ቪዲዎችና ጌሞችን የሚጫወቱ ልጆች የበለጠ ቍጣና ጥላቻ የሚያሳዩ ይሆናሉ፡፡ልጆች ያለ ገደብ ቴክኖሎጂ ከተጠቀሙ የአእምሮ ዕድገታቸው ይጎዳል፡፡የትምህርት አቀባባል ድክመት ያጋጥማቸዋል፡፡ላልተፈለገ የሰውነት ውፍረት ያጋልጣል፡፡ ለማሰታወስ ችግር ያጋጥማችዋል፡፡የቴክኖሎጂ ሱሰኛ ያደርጋል፣የእንቅልፍ እጦት ያጋጥማቸዋል፡፡
የልጆች ሥነ- ምግባርና መንፈሳዊ ሕይወት በምን ምክንያት ሊበላሽ ይችላል-?
በቂ ቁጥጥር ካለማድረግና ወላጅ ልጆቹን ሥነ-ምግባር ስለማያስተምር ታላላቆቻቸው እና ቤተሰቦቻቸው ሥነ-ምግባርን በማስተማር ረገድ ደከሞች በመሆናቸው፡፡ ሕፃናቱ አብረው የሚውሉት አብረው የሚማሩት ሰው ማንነት እንዲሁም የሚውሉበት አካባቢ መጥፎ መሆን ለእነርሱ የማይገቡ የማይመጥኑአቸውን ፊልሞችና ድርጊቶች ስለሚመለከቱ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ሥነ- ምግባርን አስመልክቶ የሚያስተላልፉት መልእክት አነሳ መሆን የሚያስፈልጋቸውን ነገሮች ባለማግኘት ምክንያት አግባብነት ወደ ሌላቸው ቦታዎች ሊሄዱ በመቻላቸው ምክንያት ነው፡፡ ልጆቻችን መከራ እንዲቋቋሙ አድርገን እናሰልጥናቸው ችግር ሲመጣ የሚቋቋሙ አናድርጋቸው፡፡ሕፃናት በማይጠቅሙ ዓለማዊ ፊልሞች ጨዋታዎች ድራማዎች፤ፍቅር ሰጥመው ካደጉ በኋ ክፉ ነገር ተው ብንል እንዴት ይቻላል? ልጆቻቸውን በሥርዓት ያስተማሩና ከቅጣት ያዳኑ ደጋግ አባቶች ነበሩ፡፡መጽሐፍ “ከእግዚእበሔር ሕግ እንዳይወጡ ሴት ልጆቻቸውንና ወንድ ልጆቻቸውንም፡አስተምረው ነበርና፤የሚቀርባቸው ክፉ ጠላት አልነበረም (፩መ.መቃቢያን፲፱፥፲፫)
 ወላጆች ለልጆቻቸው የእግዚአብሔርን ድንቅ ተኣምራት ፤የጻድቃንና የሰማዕታት ገድልና የሀገራቸውን ታሪክ በሚገባቸው መጠን እያስጠኑ የማሳደግ ኃላፊነት አለባቸው፡፡ከወላጅ ወደ ልጆች መተላለፍ የነበረበት የቃል ትምህርት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየደበዘዘ በመምጣቱ በትውልዱ ዘንድ ክፍተቱ እየበዛ መጥቷል፡፡በጥንቱ ባሕል መሠረት ልጆች ወላጆቻቸውን ቁመው ማብላት ነበረባቸው፡፡በእራት ጊዜ የእንጨት መብራት ይዞ ያበላ ነበር፡፡ይህም ቢሆን ልጅ ለወላጅ ያለውን አክብሮት ለመግለጽ የሚደረግ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጥንተ መሠረት ያለው ነው፡፡(ሉቃ፲፯፥፰፤፳፪፥፳፯)
ወላጆች ልጆቻቸውን በሥነ-ምግባር ኮትኩተው በሥነ ሥርዓት አስተምረው የማሳደግ ኃላፊነት እንዳለባቸወ ሁሉ ልጆችም ወላጆቻቸውን የመታዘዝ፤የማክበር ግዴታ አላባቸው፡፡ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ”ልጆች ሆይ ይህ ለጌታ ደስ የሚያሰኝ ነውና ለወላጆቻችሁ ታዘዙ”ይላል( ቈላ፫፥፳)ከሁሉ በፊት እናትና አባቱን የሚያከብር ልጅ ዕድሜው ይረዝማል(ዘጸ፳፥፲፪) ምክንያቱም ይመረቃልና፡፡ወላጆቹ የመረቁት ልጅ በእግዚአብሔር ዘንድም የተወደደ ነው፡፡ በመንፈሳዊና በምድራዊ ሀብት የበለጸገ ይሆናል፡፡”ምርቃት ትደርስህ ዘንድ ቢጠራህ አቤት ቢልክህ ወዴት ብለህ አባትህን አክብረው “(ሲራ፫፥፱) በታዛዥነታቸው፤በትሕትናቸው በወላጆቻቸው ከተመረቁት መካከል ያዕቆብንና ርብቃን ለአብነት ማንሳት ይበቃል (ኩፋ፳፥፷፭፤ዘፍ፳፬፥፷ ፤ኩፋ ፲፬፥፴፱)
ዲድስቅልያ አንቀጽ ፲፩፥፩ ”እናንትም አባቶች የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ይጠብቁ ዘንድ የክርስቶስን ጎዳና ይከተሉ ዘንድ ልጆቻችሁን አስተምሯቸው እጅ ሥራ አገልግሎት ይማሩ ዘንድ እዘዟቸው ሥራ ፈት ሁነው እንዳይቀመጡ”ይላል፡፡ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ሚያዝያ 23 ቀን 1982 ዓ.ም በሻሸመኔ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ተገኝተው ሲያሰተምሩ ”ልጆቻችሁ ከመዝሙር ጋር ደግሞ ሃይማኖታቸውን ፤ሥነ ምግባራቸውን እንዲማሩ ያስፈልጋል፡፡ወደ ቤተ ክርስቲያን ስትመጡ ልጆቻችሁን ይዛችሁ ኑ ብቻችሁን ከመጣችሁ የምተሠሩትን አያውቁም፤ወደየት እንደ ሄዳችሁም አያውቁም፡፡ወራሾቻችሁም አይሆኑም ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን ስትመጡ ልጆቻችሁን ይዛችሁ ኑ፤ሥዕሉን ይሳሙ፤ቅዳሴ ጠበሉን ይጠጡ ፡በእምነቱ አሻሹአቸው መስቀል እንዲሳለሙ አስተምሯቸው ዕጣኑንም ያሽትቱ የሚታጠነውን፤ሥጋወደሙን ይቀበሉ፤ቃጭሉን ይስሙ፤ደወሉ ሲደወል ይስሙ፤ቄሳቸው ማን እንደሆነ ቤተ ክርስቲያናቸው ማን እንደሆነች በውስጧም ምን ምን እንደሚሠራ ያጥኑ ፤ይማሩ፡፡ ወደ ሰንበቴም ስትሄዱ ይዛችኋቸው ግቡ ወደ ሰንበቴም ዳቦውን ተሸክመው ይምጡ እነርሱም ነገ ይህንን እንዲወርሱ የነገ ባለ አደራዎች መሆናቸውን እንዲያውቁ፡፡መመካት አይገባም የሚገባ ቢሆን እኛ ከዓለም ሁሉ የበለጠ መመካት ይገባን ነበር፡፡ምከንያቱም አባቶቻችንና እናቶቻችን ሥርዓታችንንና እምነታችንን ሁሉ ሰፍረው ቆጥረው ያስቀመጡልን ስለሆነ፤ይህ ትውልድ ይህንን ከቀበረ በኋላ ይህንን ካጠፋ በኋላ እንደገና ቤተ መዘክር እንዳይሄድ ነው ሃይማኖቱን ፍለጋ፤ታሪኩን ፍለጋ፤ስለዚህ እምነታችሁን፤ሥርዓታችሁንና መንፈሳዊ ውርሳችሁ እንድትጠብቁ አደራዬ የጠበቀ ነው”ብለው ነበር፡፡
ምንጭ፤ሐመር መጽሔት ፳፮ኛዓመት ቊ ፮ ጥቅምት ፳፻፲ወ

አንቲ ውእቱ ጽጌ መዓዛ ሠናይ (ውዳሴ ማርያም ዘእሑድ)


                                      መ/ር ዘለዓለም ሐዲስ
ከመስከረም ፳፮ እስከ ኅዳር ፭ ያለው ዘመን ወርኀ ጽጌ በመባል ይታወቃል፡፡ወርኀ ጽጌም የተባለበት ምክንያት ዕፀዋቱ አብበው ምድርን በአበባነታቸው አሸብርቀው የሚታዩበት ወር በመሆኑ ነው፡፡ጽጌ ማለት ጸገየ አበበ ካለው የግእዝ ሐረግ የተመዘዘ ሲሆን ጽጌ ትርጉሙ አበባ ማለት ነው ጌታችን በጽጌ መስለው የተናገሩ ነቢያት ናቸው ከዐበይት ነቢያት አንዱ የሆነው ኢሳይያስ ጌታን ከዕሤይ ሥር በትር ትወጣለች ከርሷም አበባ ይገኛል በማለት ጌታን በአበባው እመቤታችን በበትር መስሎ ተናግሯል፡ንጉሥ ሰሎሞንም በመኃልዩ“ጽጌ አስተርአየ በውስተ ምድርነ በምድራችን አበባ ታየ”በማለት ጌታን በአበባ እመቤታችን በምድር ይመስላታል(ኢሳ ፲፩፥፩)
የዘመነ ሐዲስ ሊቃውንትም የነቢያትን ምሳሌያዊ ምስጢር ከማብራራታቸው በተጨማሪ እመቤታችን በጽጌ በአበባ፣ልጇን ከአበባው በሚገኘው ፍሬና መዓዛ መስለው ተናግረዋል ከእነዚህ ሊቃውንት መካከል አንዱ የሆነው ቅዱስ ኤፍሬም “አንቲ ውእቱ ጽጌ መዐዛ ሠናይ እንተ ሠረጸት እምሥርወ ዕሤይ ከዕሤይ ሥር የተገኘች መዓዛዋ ያማረ ጽጌ አንቺ ነሽ በማለት እመቤታችን በአበባ (በጽጌ) ልጇን በመዓዛው መስሎ ተናግሯል ሌሎችም ሊቃውንት ተመሳሳይ ምሳሌ በመመሰል ምስጢረ ሥጋዌውን አብራርተዋል፡፡
ይህ ወራት በቀደሙት አባቶቻችን ዘንድ እስከ ፲፫ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ዘመነ ጽጌ እየተባለ እግዚአብሔር ምድርን በአበባ ማስዋቡ በቤተ ክርስቲያን ቢዘከርም እንደ አሁኑ ማኅሌተ ጽጌ ሰቆቃወ ድንግል እየተቆመ የእመቤታችን ስደት አይታሰብበትም ነበር፡፡ወቅቱ እግዚአብሔር ምድርን በአበባዎች የሚያስጌጥበት ስለሆነ ቅዱስ ያሬድ በዚህ ወቅት ምድር በአበባ የሚያስውቡትን የሽቱ ዕፀው ናርዶስ ቀንሞስ ሮማን የመሳሰሉትን እያነሣ ምድር በእነዚህ ሁሉ አበባዎች እንዳጌጠችና እንደተዋበች የተናገረውን የየየቀኑን መዝሙር እየዘመረች ቤተ ክርስቲያናችን እግዚአብሔርን ታመሰግንበት ነበር፡፡በኋላ ግን ከቅዱስ ያሬድ ቀጥለው የተነሱት ሊቃውንት ስለእመቤታችን መሰደድ ድርሰት የደረሱ ሊቃውንት የነቢያትን ምሳሌ መነሻ በማድረግ እመቤታችን አበባውን በሚያስገኙ ያማሩ ያማሩ የሽቱ ዕፀው፣ልጇን በጽጌ በአበባ እየመሰሉ ማኅሌተ ጽጌና ሰቆቃወ ድንግልን ከደረሱ ማኅሌቷንም መቆም ከጀመሩ በኋላ ወርኃ ጽጌ ተብሎ ከመታሰቡ በተጨማሪ የእመቤታችን የስደቷ መታሰቢያ ሁኖ መከበር ጀምሯል፡፡
በ፲፫ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በአባ ዜና ማርቆስ አስተማሪነት ከአይሁዳዊነት ወደ ክርስቲያንነት የተመለሰው አባ ጽጌ ብርሃንና (ጽጌ ድንግል) አባ ገብረ ማርያም መምህር ዘደብረ ሐንታው ሁለቱ ማኅሌተ ጽጌንና ሰቆቃወ ድንግልን ደርሰው የእመቤታችን ስደት እያሰቡ ማኅሌት መቆም ከጀመሩበት ከ፲፫ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ማኅሌቱ ሳይቋረጥ ቀጥሏል፡፡ምእመናንንም የእመቤታችን ስደት ለማስታወስ በእመቤታችን ስም ማኅበር እየጠጡ ምንም ጾሙ የፈቃድ ቢሆንም ጾም እየጾሙ ዝክር እየዘከሩ ያከብሩታል ማኅበሩም የሚጠጣው በቤተ ክርስቲያን ወይም በተራራ ላይ ነው ከቤታቸው የማይጠጡበት ምክንያት እመቤታችን በረሃ ለበረሃ ስለተሰደደች ያንን ለማስታወስና እንደ እመቤታችን በመንገድ የደከመን እንግዳ ለመቀበል ነው፡፡
የማኅሌተ ጽጌ ደራሲ የሆነው አባ ጽጌ ብርሃን (ድንግል) ከመጠመቁ በፊት ዘካርያስ ተብሎ ይጠራ ነበር ለማመን ያበቃችውም ገባሪተ ኃይል የሆነች የእመቤታችን ሥዕል ናት ብዙ ተአምራትን ስታደርግ ስላየ ወደአባ ዜና ማርቆስ በመሔድ ተምሮ ለማመን በቅቷል ከአባ ዜና ማርቆስ ትምህርተ ሃይማኖትን ተምሮ በምንኵስና ሕይወት መኖር ከጀመረ በኋላም ያችን ለማመን ያበቃችውን ገባሪተ ኃይል ሥዕል ሳይሳለም አይውልም ነበር፡፡
ከሥዕሏ ፊትም ሲቆም የሚያቀርበው እጅ መንሻ (መባዕ) ስለሌው ይጨነቅ ነበር በኋላ ግን ይህ ዘመነ ጽጌ ሲደርስ በየቀኑ ሃምሳ ሃምሳ የጽጌረዳ አበባ እየፈለገ እንደ ዘውድ እየጎነጎነ ለዚያች ምስለ ፍቁር ወልዳ ሥዕል ያቀዳጃት ነበር በጋው ሲወጣ የጽጌረዳው አበባ ስለደረቀበት ከሥዕሏ ተንበርክኮ እመቤቴ በየቀኑ የማመጣልሽ የጽጌረዳ አበባ ደረቀ ስለአበባው ፈንታ መልአኩ ተፈሥሒ ተፈሥሒ እያለ ያመሰገነሽን ምስጋና በአበባው ቁጥር ልክ ሃምሳ ሃምሳ ጊዜ እንዳመሰግንሽ ፍቀጅልኝ በማለት ተማጸነ ከዚህ በኋላ በየቀኑ ተፈሥሒ ፍሥሕት የሚለውን የመልአኩን ምስጋና በየቀኑ ሲያቀርብላት ምስጋናው እንደጽጌረዳ አበባ እየሆነ ከአንደበቱ ሲወጣ እመቤታችን አበባውን እየተቀበለች ስትታቀፈው ሰዎች እያዩ ያደንቁ እንደነበር ገድለ ዜና ማርቆስ ያስረዳል፡፡
እሱም በድርሰቱ እንዲህ ሲል ገልጾታል“አባዕኩ ለኪ ስብሐተ ተአምር ዘይሤለስ በበሃምሳ ህየንተ ጽጌያት ሃምሳ ለስዕልኪ አክሊለ ርእሳ” ለስዕልሽ ዘውድ ይሆን ዘንድ ሃምሳ የጽጌ ረዳ አበባ አቀርብልሽ ስለነበረው ፈንታ ሦስት ጊዜ ሃምሳ(መቶሃምሳ) የሚሆን ምስጋናን አቀረብኩልሽ በማለት፡፡ስለዚህ ዘመነ ጽጌ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ እግዚአብሔር ምድርን በአበባ ማስጌጡን ማሰባችን እንዳለ ሁኖ በተጨማሪ የእመቤታችን የስደቷን በዓል እናስብበታለን፡፡
                                           ስለምን ወደግብፅ ተሰደደ?   
ጌታችን ከመወለዱ በፊት ከጽንሰቱ እስከ ዳግም ምጽአቱ ድረስ ስለሚሠራው ሥራ አስቀድሞ በነቢያቱ እያደረ ትንቢት አናግሯል፡፡ መልአኩም ለዮሴፍ ብላቴናውን ሄሮድስ እንደሚገድለው ሲነግረው የሚሸሽበትን ቦታ ሳይቀር “ተንሥእ ንሣእ ሕፃነ ወእሞ ወሑር ውስተ ብሔረ ግብፅ” ተነስተህ እናቱንና ብላቴናውን ይዘህ ወደግብፅ ሽሽ በማለት ለስደቱ ግብፅን እንደመረጣት በትንቢቱ ተናግሯል(ማቴ፪፥፲፫) ከደቂቅ ነቢያት አንዱ ሆሤዕም ጌታችን ወደግብፅ እንደሚሰደድ “እምግብፅ ጸዋእክዎ ለወልድየ ልጄን ወደግብፅ ጠራሁት” ሲል ልዑለ ቃል ኢሳይያስ ደግሞ “ወይወርድ እግዚእነ ውስተ ምድረ ግብፅ እንዘ ይጼዐን ዲበ ደመና ቀሊል፤ጌታችን በፈጣን ደመና (በእመቤታችን ጀርባ) ተጭኖ ወደግብፅ ይወርዳል በማለት ተናግሯል (ሆሴ፲፩፥፩ ኢሳ ፲፱፥፩)ከሌሎች ሀገሮች ለስደቱ ግብፅ የተመረጠችበት ምክንያቱ ብዙ ቢሆንም ጥቂቶቹን እንመለከታለን፡፡
፩.ለፍቅሩ ስለሚሳሱለት፤ ጌታችን ወደግብፅ የተሰደደበት ምክንያት ግብፃውያን ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ጌታችን ከምንም በላይ ለፍቅሩ ይሳሱለት ስለነበረ ነው፡፡ይህንም ወደ ግብፅና ወደ ኢትዮጵያ በተሰደደ ጊዜ ግብፃውያንና ኢትዮጵያውያን እንዴት አክብረው እንደተቀበሉትና እንደሳሱለት በነገረ ማርያም የተጻፈው ታረክ ጥሩ ማስረጃ ነው ምንም ሰይጣን ያደረባቸው እነ ኮቴባን የመሰሉ አንዳንድ ክፉ ሰዎች ቢያጋጥሟቸውም ብዙዎቹ ደግሞ ለፍቅሩ በመሳሳት“ደም ግባቱ ከሰው ልጆች ሁሉ ያምራል”ተብሎ የተነገረለትን መልኩን በማየት ብቻ ለማመን የበቁ ደጋጎች ነበሩ እንኳን ቤት መስርተው በዓለም የሚኖሩት በበረሃ ውስጥ የሚኖሩ ሽፍታዎችም ለጌታችን ያሳዩት ርኅራኄና ፍቅር የተለየ ነበር፡፡ሕፃኑ ኢየሱስ ክርስቶስና እመቤታችን ዮሴፍና ሰሎሜ ኢየሩሳሌምን ለቀው ወደ ግብፅ ሲሰደዱ ግብፃዊው ጥጦስና አይሁዳዊ ዳክርስ ሁለት ወንበዴዎች በረሃ ውስጥ አግኝተዋቸው ነበር እስራኤላዊዉ ዳክርስ ልብሳቸውን ለመግፈፍ ሲፋጠን ግብፃዊዉ ጥጦስ ግን በልቡናው ርኅራኄ አድሮበት ለፍቅሩ በመሳሳት እነዚህ ሰዎች የቤተ መንግሥት ሰዎች ናቸው አሳዘኑኝ ወደ ዚህ ቦታ የመጡት ያለ ምክንያት አይሆንምና አንቀማቸው እንተውላቸው በማለት ለጌታ ያለውን ፍቅርና ርኅራኄ ገልጧል
ወደ ኢትዮጵያም በመጡበት ወራት ቤታቸውን እየለቀቁ ያስተናግዷቸው እንደ ነበር ድርሳነ ዑራኤል በሰፊው ይናገራል እመቤታችንም የኢትዮጵያ ሰዎች ባሳዩአት ፍቅር ስትደሰት ጌታችን የዐሥራት ሀገር ትሁንሽ ብሎ ሀገሪቱን ለእመቤታችን የሰጣት በወቅቱ የነበሩት ኢትዮጵያውያን ባሳዩት ደግነትና ርኅራኄ ነው፡፡ደጉ አባት አብርሃም እንግዳ በመቀበሉና ደግ በመሆኑ ሥላሴ ከቤቱ እንደ ገቡለት ሎጥም እንግዳ በመቀበል መላእክት ወደ ቤቱ ገብተው ሰዶምና ገሞራ ሲጠፉ ከጥፋት እንደታደጉት ጌታችን አባቶቻችን ባደረጉት ደግነት ኢትዮጵያ በእመቤታችን ምልጃ ሊጠብቃት ስለፈለገ የዐሥራት ሀገር አድርጎ ሰጣት ምን ጊዜም ሊምረው የወደደውን ሰው የእመቤታችን ፍቅር ያሳድርበታልና እመቤታችን እንድንወድ አድርጎ በአማላጅነቷ እንድንጠበቅ ፈቀደልን ጌታችን ወደ ግብፅና ወደ ኢትዮጵያ የተሰደደበት ምክንያት ለፍቅሩ ይሳሱለት ለነበሩት ኢትዮጵያና ግብፅ በፍቅር ለመገለጽ ሲሆን በተጨማሪም ገዳማተ ግብፅንና ገዳማተ ኢትዮጵያንም ለመባረክ ጭምር ነው፡፡በግብፅና በኢትዮጵያ ያሉ ታላላቅ ገዳማት የተባረኩት በስደቱ ወራት ነውና፡፡
ኪዳነ መልከ ጼዴቅን ለመፈጸም ነው፤መልከ ጼዴቅ ከዘመዶቹ ተለይቶ በምናኔ ሲኖር በሚያቀርበው መሥዋዕት በሚጸልየው ጸሎት በሥጋ ዘመዶቹ የሆኑትንና የማይዘመዱትን እንዲምርለት እግዚአብሔርን ይለምነው ነበር እንዲህ እያለ አቤቱ ለዲያብሎስ ከመገዛት ለአንተ ወደ መገዛት መልሰኸኛልና ከሀገሬም አውጥተህ አንተን ወደማመልክበት ቦታ አምጥተኸኛልና በደሌንም ይቅር ብለህልኛልና አመሰግንሃለሁ ነገር ግን እኔን ይቅር እንዳልከኝ ዘመዶቼንም ማርልኝ፡፡እግዚአብሔርም ልመናውን ተቀብሎ እንዲህ ሲል ድምፁን አሰምቶታል ልጄን ወደ ግብፅ በጠራሁት ጊዜ ዘመዶችህን እምርልሃለሁ ብሎ ቃለ ኪዳን ገብቶለት ነበር ዘመኑ ሲደርስ የተናገረውን የማያስቀር እግዚአብሔር የገባለትን ቃለ ኪዳን ለመፈጸም ወደግብፅ ተሰደደለት (ተረፈ ቄርሎስ ፳፭፥፩—፱) ኖኅ ከጥፋት ውኃ በኋላ መልአከ እግዚአብሔርን ከመካከላቸው እንደ ዳኛ አስቀምጦ ለሦስቱ ልጆቹ ለሴም ለካም ለያፌት ይህን ዓለም ቀኝ ቀኙን ለሴም መሀሉን ለያፌት ግራ ግራውን ለካም አውርሷቸዋል መልከ ጼዴቅ ትውልዱ ከካም ወገን ስለሆነ ምንም ዘመዶቼን ማርልኝ ብሎ የጸለየ ለሁሉም ዘመዶቹ ቢሆንም የአባቱ ወገኖች የካም ዘሮች ናቸውና ጌታ ወገኖቹን ሊምርለት ቃል ኪዳኑን ሊፈጽምለት ወደግብፅ ተሰዷል
.አጋንንትን ከግብፅና ከሰው ልቡና አስወጥቶ ለመስደድ ነው
ጌታ ገና ከመወለዱ በፊት ለልደቱ ሃያ አራት ቀን ሲቀረው መካነ ልደቱ ቤተ ልሔምን በመላእክት አስጠብቋት ነበር፡፡በዚህ ጊዜም አጋንንት በመላእክት ረቂቅ ጦር እየተወጉ ኢየሩሳሌምን ለቀው ሲወጡ የተሰደዱት ወደ ግብፅ ነበር አጋንንት በውስጣቸው አድርው ይመለኩባቸው የነበሩ ጣዖታትም ተሰባብረው ጠፍተዋል ይህንንም ጌታ ወደ ግብፅ በተሰደደ ጊዜ ራሳቸው አጋንንት በኢየሩሳሌም ማደሪያ እንዳሳጣኸን በዚህም ልታሳድደን መጣህን ብለው እንደ መሰከሩ በነገረ ማርያም ተጽፏል ጌታ ወደግብፅ የተሰደደበት ሦስተኛው ምክንያት እነዚህ አጋንንት ማደሪያ ካደረጓቸው የሰው ልቡናናና ከጣዖቱ አስወጥቶ በመስደድ አጋንንትን ለማሳደድ ነው፡፡ ይህንም ቴዎዶጦስ የተባለው ሊቅ ጌታ ተሰደደ ሲባል ብትሰማ ፍጡር ነው ብለህ አትጠራጠር ፈርቶ ሸሸም አትበል የጌታ መሰደድ ዲያብሎስን ከሰው ልቡና አስወጥቶ ለማሳደድ እንደሆነ እመን እንጅ ብሎ የተሰደደ ዲያብሎስን ለማሳደድ መሆኑን ገልጧል (ተረፈ ቄር፲፥፭)ይህ ሊቅ ጌታ የተሰደደው ዲያብሎስን ለማሳደድ ብቻ ሳይሆን ሰው መሆኑን ለሚጠራጠሩ፣ምትሐት ነው ለሚሉትም በትክክል ሰው መሆኑን ለማስረዳት እንደ ተሰደደ በዚሁ ምዕራፍና ቁጥር ይገልጻል ሰው ባይሆን ኑሮ አይሰደድም ነበር ፡፡
.አዳም ከዚህ ዓለም አፍአ በምትሆን ከገነት ተሰዶ ነበርና ለመካስ
ጌታችን በዕለተ ልደቱ የበለስ ቅጠል የለበሰ አህዮችና ላሞች እስኪያሟሙቁት ድረስ የተበረደ አዳም ከገነት ሲወጣ የበለስ ቅጠል ስለለበሰ ከልብሰ ብርሃን በመገፈፉ ስለተበረደ አዳም የተቀበለውን መከራ ተቀብሎ ለመካስ ነው፡፡ገና በሁለት ዓመቱ ከኢየሩሳሌም ወደግብፅ የተሰደደውም ከዚያው ሁኖ መዳን ተስኖት ሳይሆን አዳም ዕፀ በለስን በልቶ ከገነት እንደ ተሰደደ እሱም ከኢየሩሳሌም ወደ ምድረ ግብፅ ተሰዶ አዳም የተቀበለውን መከራ ተቀብሎ ለመካስ ነው፡፡አዳም ከገነት ወደ ማያውቀው ወደዚህ ዓለም ሲሰደድ ብዙ ፍዳና መከራ አግኝቶታል ፡ከአንዱ ቦታ ወደ አንዱ ቦታ በሚያደርገው እንቅስቃሴ እሾሁ ሲወጋው እንቅፋቱ ሲመታው ይህ ሁሉ የደረሰበት ከፈጣሪዉ ትእዛዝ በመውጣቱ መሆኑን ሲያስብ ዕንባው ከዓይኑ ያለማቋረጥ እንደምንጭ ውኃ ይፈስ ነበር፡፡
በገነት ሳለ የሚበላውና የሚጠጣው ከሰውነቱ ጋር ተዋሕዶ ይቀር ነበር እንጅ ወደ ኀሠርነት ስለማይለወጥ በልቶ ጠጥቶ መጨነቅ ሆድ ቁርጠት በልቶ መታመም በቁንጣን መሰቃየት አልነበረበትም ከገነት ከወጣ በኋላ ግን ይህ ሁሉ መከራ በርሱ ላይ መጥቶበታል ይህን ሁሉ መከራ ስለተቀበለ አዳም ወደዚህ ዓለም ሲሰደድ የተቀበለውን መከራ ተቀብሎ ሊክሰው ስለወደደ ወደ ግብፅ ተሰደደለት እንደተበረደ ተበረደለት በዕፀ በለስ ምክንያት ከገነት እንደወጣ በዕፅ ተሰቅሎ ያጣው ክብሩንና የክብር ቦታውን ገነትን መለሰለት
፭ ለሰማዕታት ስደትን ለመባረክ ፤ሰማዕትነት እሳትና ስለት ብቻ አይደለም ሀገርን ጥሎ መሰደድም ሰማዕትነት ነው፡፡ በመሆኑም ለሰማዕታት ስደትን ለመባረክ የማትችሉት መከራ ቢመጣባችሁ ተሰደዱ ለማለት ወደ ግብፅ ተሰደደ ስደት ከሰማዕትነት ገብቶ የተቆጠረበት ምክንያት መከራው በሰይፍ ተቆርጦ በስለት ተቀልቶ ከመሞት በላይ ስለሆነ ነው፡፡ከመከራ ሁሉ ከባዱ መከራም ደም ሳይፈስ በየጊዜው የሚፈጸመው የሰማዕትነት ተጋድሎ ነው በሰይፍ ተቀልቶ እሳት ውስጥ ገብቶ መሞት ቀላል ነው ባይባልም አስፈሪ ቢሆንም በስደት ልዩ ልዩ መከራ ከመቀበልና በየጊዜው ከመፈተን ግን የተሻለ ነው ሰይፍ የሚያስፈራው ለተወሰነ ደቂቃ ነው ስደት ግን በየጊዜው ከሰይፍ በላይ በሚያም መከራ መቆረጥና መሰቃየት ነው እመቤታችን በስደቷ ጊዜ ልጇ እንዳይሞትባት ከሰው ለመሰወር በበረሃው ስትሔድ ግሩማን አራዊት ያስደነግጧት ነበር ሰው ወዳለበት መንደር ስትሔድ ሰዎች ይጣሏታል፡፡
በዚያ ላይ ደግሞ ቀን ሐሩረ ፀሐዩ ሌሊት ቁረ ሌሊቱ እየተፈራረቀባት እሾሁ እየወጋት እንቅፋቱ እየመታት መውጫና መግቢያው በማይታወቅ በረሓ ውስጥ ገብቶ መሰቃየቱ የመንገዱ መጥፋት በዚያ አሰልችና አድካሚ ጉዞ ውስጥ የልጇ በውኃ ጥም መቃጠልና ማልቀስ ለእመቤታችን ሌላው ሰማዕትነት ነበር ይህን ሁሉ መከራ መቀበሏ ግን ሰማዕታትን በስደትና በልዩ ልዩ መከራ ሲሰቃዩ መከራውን እንዲችሉ ያደርጋቸዋል፡፡ለምን ይህ ሁሉ መከራ አገኘን ብሎ ተስፋ እንዳይቆርጡ ተስፋ ይሆናቸዋል ስለዚህ ለምን ይህ ሁሉ መከራ ደረሰብን ብለው ተስፋ እንዳይቆርጡ እመቤታችን ከተወደደ ልጇ ጋር ስደትን ባርካ ሰጠቻቸው እሷን መሠረት አብነት በማድረግም ብዙ ቅዱሳን ለሃይማኖታቸው ለቤተ ክርስቲያናቸው በስደትና በስለት መከራ ተቀበሉ ዋሻ ለዋሻ በረሓ ለበረሓ ተንከራተቱ ግን ተስፋ አልቆረጡም እመቤታችን መጽናኛ ሁናቸዋለችና ስለዚህ እመቤታችን በስለት ከሚፈጸመው መከራ ውጭ ያልተቀበለችው መከራ ስለሌለ እሞሙ ለሰማዕት የሰማዕታት እናታቸው እየተባለች ትመሰገናለች(ቅዳሴ ማርያም)
የቅዱሳንን ገድልና መከራ የሚናገረው ስንክሳር የቤተ ክርስቲያናችን መጽሐፍም ስደት እሳትና ስለት ብቻ አለመሆኑን እየተሰደዱ እየታሠሩ እየተገረፉ መከራ የሚቀበሉትን ቅዱሳን ሰማዕት ዘእንበለ ደም እያለ ይጠራቸዋል ሰማዕት ዘእንበለ ደም ማለትም ደማቸው ሳይፈስ ሰማዕትነትን የተቀበሉ ማለት ነው፡፡የእነዚህ ሰማዕታት ሰማዕትነት አንድ ጊዜ በማይገድል በየጊዜው በሚደርስ መከራ መሰቃየት ነውና፡፡
        በስደቷ ጊዜ ያገኛት መከራ
እመቤታችን ከተወደደ ልጇ ጋር በተሰደደችበት ጊዜ ልዩ ልዩ መከራ አግኝቷታል፡፡መከራውም ለእመቤታችን ኀዘን ጭንቅ ቢሆንም ለእኛ ግን ደስታና ድኅነት ነበር ምክንያቱም ከእመቤታችን በኋላ የነበሩ አባቶቻችንና የነርእሱ ልጆች የሆንነው እኛ ዛሬ ላይ ስደቷን መከራዋን እያሰብን የቻልን ሰውነታችን በጾም እያደከምን ያልቻልን ማኅሌት እየቆምን ለርሷና ለልጇ የምስጋና እጅ መንሻ እያቀረብን በስደቷ ወራት የደረሰባትን መከራ እያዘከርን እንድታማልደን እንማጸንበታለን በረከትም እናገኝበታለን፡፡ አባ ሕርያቆስ በቅዳሴ ማርያም ድርሰቱ ላይ “አዘክሪ ድንግል ንግደቶ ዘምስሌኪ እንዘ ትጐይዪ ምስሌሁ እሀገር ለሀገር በመዋዕለ ሄሮድስ ርጉም አዘክሪ ድንግል አንብዐ መሪረ ዘውኅዘ እምአዕይንትኪ ወወረደ ዲበ ገጸ ፍቁር ወልድኪ አዘክሪ ድንግል ረኀበ ወጽምዐ ምንዳቤ ወኀዘነ ወኵሎ ዐፀባ ዘበጽሐኪ ምስሌሁ፤ርጉም ሄሮድስ በነገሠበት ወራት ከአንቺ ጋር ከአንዱ ሀገር ወደ አንዱ ሀገር የተሰደደውን መሰደድ አሳስቢልን በአይኖችሽና በልጅሽ ፊት የወረደውን መሪር ዕንባ አሳስቢልን ረሀቡን ጥሙን ችግሩንና ኀዘኑን ያገኘሽንም ልዩ ልዩ መከራ አሳስቢልን (ቅዳሴ ማርያም)በማለት እመቤታችን ሔሮድስ በነገሠበት ወራት ከአንዱ ሀገር ወደሌላው ሀገር መሰደዷን፣ ከዓይኗ የፈሰሰውንና በልጇ ፊት የወረደውን ዕንባ አማላጅ አድርጋ እንድታሳስብልን ይናገራል ይህንም ቃል ቅዳሴ ማርያም በተቀደሰበት ቀን ቤተ ክርስቲያናችን ሁልጊዜ ካህናቱ ሥጋውን ደሙን አቀብለው ከተመለሱ በኋላ ትጸልየዋለች እኛን ኀጥአንንም ታማልድበታለች፡፡
እመቤታችን በተሰደደችበት ወራት ካጋጠማት ጭንቅ ጭንቅ መከራ ሁሉ የሚበልጠው በልጇ ላይ የሚመጣው መከራ ነበር ምክንያቱም ሀገር ጥላ የተሰደደችው ተወዳጁን ልጇን ከሞት ለማዳን ነውና፡፡ሄሮድስ አራት ወታደሮችን ከነሠራዊታቸው በሽልማት ሸልሞ እመቤታችን ከነልጇ ይዘው ከመጡ የበለጠ ሹመትና ሽልማት እንደሚጠብቃቸው አብስሮ ልኳቸው ነበር፡፡
የዮሴፍ ልጅ ዮሳ ይህንን ምስጢር ለአባቱ ለዮሴፍና ለእመቤታችን እንዲሁም ለሰሎሜ ለመንገር ከነበረው ኃይል ላይ የአንበሳ ኃይል ተጨምሮለት በፍጥነት ሲጓዝ እያለ የመልካም ነገር ጠላት የሆነው ሰይጣን መንገድ ላይ ጠብቆ ወዴት እንደሚሔድ ጠየቀው ዮሳም በየዋህነት የሚሮጥበትን ጉዳይ ሳይደብቅ ዘርዝሮ ነገረው ሰይጣንም የሄሮድስ ሠራዊት ቀድመው መሔዳቸውን በሔዱበት ፍጥነት ካገኟቸው እንደሚገድሏቸው ዮሳም በከንቱ እንዳይደክም ያዘነ በሚመስል ድምፅ እንዲመለስ ነገረው ዮሳ ግን ሐሳቡን ሳይቀበል ከሞቱም እቀብራቸዋለሁ በሕይወት ካሉም የሆነውንና የታሰበውን ነግሬ እንዲሸሹ አደርጋለሁ ብሎ መገስገስ ጀመረ ኃይል ከእግዚአብሔር ተጨምሮለታልና፡፡
ዮሳ እየሮጠ ሲሔድ መንገድ ላይ አገኛቸውና ገና ከመድረሱ እመቤታችን ያስደነገጠ ሕሊናዋን የረበሸ ምርር ብላም እንድታለቅስ የሚያደርግ አሰቃቂ ዜናን ነገራት እመቤታችንም የዮሳን ቃል ሰምታ ከአንዱ ሀገር ወደ ሌላኛው ሀገር የተሰደድኩት ከሞት ላላድንህ ነውን? ልጄ አንተን ሲገሉህ ከማይ እኔ አስቀድሜ ልሙት በማለት ስታለቅስ ሕፃኑ ኢየሱስ ክርስቶስ በእጁ ዕንባዎቿን በማበስ እንደማይሞት ከነገራት በኋላ ፊቱን ወደ ዮሳ መልሶ ዮሳ ዕሡይ ምጽአትከ (አመጣጥህ ዋጋ የሚያሰጥ መልካም) ነበር ነገር ግን እናቴን አስደንግጠሃታልና በዕለተ ምጽአት አስነሥቼ ዋጋህን እስከሰጥህ ድረስ ይህችን ደንጋይ ተተንተርሰህ ዕረፍ ብሎት ዐርፋል፡፡
እንግዲህ እመቤታችን በስደቷ ወራት ውኃ በመጠማት በመራብ እሾሁ እየወጋት እንቅፋቱ እየመታት ቀን የበረሓው ሐሩር እያቃጠላት ሌሊት ደግሞ ብርዱ እያሳቃያት ትጓዝ ስለነበር ያገኛትን መከራ በቃላት ገልጾ መጨረስ አይቻልም በተለይ ሰው ስታይ ልጇን የሚገድሉባት ስለሚመስላት በጣም ትጨነቅም ታለቅስም ነበር፡፡
አባ ሕርያቆስም በስደትሽ ወራት ያገኘሽን ልዩ ልዩ መከራ ከልጅሽ ዘንድ አሳስቢልን ያለው ያገኛትን መከራ አስባ እኛንም ከአስፈሪ ፈተና እንድታወጣን ነው አባቶችም እመቤታችን መከራዋን እያነሡ ካለቀሱና ከለመኗት ፈጥና እንደምትሰማ በሕይወታቸው ካገኙት ተሞክሮ ተነሥተው ይናገራሉ፡፡ስለዚህ እኛም በወርኀ ጽጌ ስደቷን ስናስብ የራሳችንንም የሀገራችንንም ችግር አብረን ልናስብ ይገባል፡፡በተለይ በሀገር የሚመጣ ችግር ለሁላችንም የሚተርፍ ስለሆነ እመቤታችን የዐሥራት ሀገሯን በአማላጅነቷ እንድትጠብቃት ሁላችንም የቻልነውን ያህል በወርኀ ጽጌ ተግተን ልንጸልይ ማኅሌት ልንቆም በጸሎት ልንበረታ ይገባል አምላካችን እግዚአብሔር የሀገራችን ጥፋት አያሳየን አሜን፡፡
ምንጭ፤ሐመር መጽሔት ፳፮ኛዓመት ቊ ፮ ጥቅምት ፳፻፲ወ፩ ዓ.ም

አንቲ ውእቱ ጽጌ መዓዛ ሠናይ (ውዳሴ ማርያም ዘእሑድ)

                                                                            መ/ር ዘለዓለም ሐዲስ
ከመስከረም ፳፮ እስከ ኅዳር ፭ ያለው ዘመን ወርኀ ጽጌ በመባል ይታወቃል፡፡ወርኀ ጽጌም የተባለበት ምክንያት ዕፀዋቱ አብበው ምድርን በአበባነታቸው አሸብርቀው የሚታዩበት ወር በመሆኑ ነው፡፡ጽጌ ማለት ጸገየ አበበ ካለው የግእዝ ሐረግ የተመዘዘ ሲሆን ጽጌ ትርጉሙ አበባ ማለት ነው ጌታችን በጽጌ መስለው የተናገሩ ነቢያት ናቸው ከዐበይት ነቢያት አንዱ የሆነው ኢሳይያስ ጌታን ከዕሤይ ሥር በትር ትወጣለች ከርሷም አበባ ይገኛል በማለት ጌታን በአበባው እመቤታችን በበትር መስሎ ተናግሯል፡ንጉሥ ሰሎሞንም በመኃልዩ“ጽጌ አስተርአየ በውስተ ምድርነ በምድራችን አበባ ታየ”በማለት ጌታን በአበባ እመቤታችን በምድር ይመስላታል(ኢሳ ፲፩፥፩)
የዘመነ ሐዲስ ሊቃውንትም የነቢያትን ምሳሌያዊ ምስጢር ከማብራራታቸው በተጨማሪ እመቤታችን በጽጌ በአበባ፣ልጇን ከአበባው በሚገኘው ፍሬና መዓዛ መስለው ተናግረዋል ከእነዚህ ሊቃውንት መካከል አንዱ የሆነው ቅዱስ ኤፍሬም “አንቲ ውእቱ ጽጌ መዐዛ ሠናይ እንተ ሠረጸት እምሥርወ ዕሤይ ከዕሤይ ሥር የተገኘች መዓዛዋ ያማረ ጽጌ አንቺ ነሽ በማለት እመቤታችን በአበባ (በጽጌ) ልጇን በመዓዛው መስሎ ተናግሯል ሌሎችም ሊቃውንት ተመሳሳይ ምሳሌ በመመሰል ምስጢረ ሥጋዌውን አብራርተዋል፡፡
ይህ ወራት በቀደሙት አባቶቻችን ዘንድ እስከ ፲፫ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ዘመነ ጽጌ እየተባለ እግዚአብሔር ምድርን በአበባ ማስዋቡ በቤተ ክርስቲያን ቢዘከርም እንደ አሁኑ ማኅሌተ ጽጌ ሰቆቃወ ድንግል እየተቆመ የእመቤታችን ስደት አይታሰብበትም ነበር፡፡ወቅቱ እግዚአብሔር ምድርን በአበባዎች የሚያስጌጥበት ስለሆነ ቅዱስ ያሬድ በዚህ ወቅት ምድር በአበባ የሚያስውቡትን የሽቱ ዕፀው ናርዶስ ቀንሞስ ሮማን የመሳሰሉትን እያነሣ ምድር በእነዚህ ሁሉ አበባዎች እንዳጌጠችና እንደተዋበች የተናገረውን የየየቀኑን መዝሙር እየዘመረች ቤተ ክርስቲያናችን እግዚአብሔርን ታመሰግንበት ነበር፡፡በኋላ ግን ከቅዱስ ያሬድ ቀጥለው የተነሱት ሊቃውንት ስለእመቤታችን መሰደድ ድርሰት የደረሱ ሊቃውንት የነቢያትን ምሳሌ መነሻ በማድረግ እመቤታችን አበባውን በሚያስገኙ ያማሩ ያማሩ የሽቱ ዕፀው፣ልጇን በጽጌ በአበባ እየመሰሉ ማኅሌተ ጽጌና ሰቆቃወ ድንግልን ከደረሱ ማኅሌቷንም መቆም ከጀመሩ በኋላ ወርኃ ጽጌ ተብሎ ከመታሰቡ በተጨማሪ የእመቤታችን የስደቷ መታሰቢያ ሁኖ መከበር ጀምሯል፡፡
በ፲፫ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በአባ ዜና ማርቆስ አስተማሪነት ከአይሁዳዊነት ወደ ክርስቲያንነት የተመለሰው አባ ጽጌ ብርሃንና (ጽጌ ድንግል) አባ ገብረ ማርያም መምህር ዘደብረ ሐንታው ሁለቱ ማኅሌተ ጽጌንና ሰቆቃወ ድንግልን ደርሰው የእመቤታችን ስደት እያሰቡ ማኅሌት መቆም ከጀመሩበት ከ፲፫ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ማኅሌቱ ሳይቋረጥ ቀጥሏል፡፡ምእመናንንም የእመቤታችን ስደት ለማስታወስ በእመቤታችን ስም ማኅበር እየጠጡ ምንም ጾሙ የፈቃድ ቢሆንም ጾም እየጾሙ ዝክር እየዘከሩ ያከብሩታል ማኅበሩም የሚጠጣው በቤተ ክርስቲያን ወይም በተራራ ላይ ነው ከቤታቸው የማይጠጡበት ምክንያት እመቤታችን በረሃ ለበረሃ ስለተሰደደች ያንን ለማስታወስና እንደ እመቤታችን በመንገድ የደከመን እንግዳ ለመቀበል ነው፡፡
የማኅሌተ ጽጌ ደራሲ የሆነው አባ ጽጌ ብርሃን (ድንግል) ከመጠመቁ በፊት ዘካርያስ ተብሎ ይጠራ ነበር ለማመን ያበቃችውም ገባሪተ ኃይል የሆነች የእመቤታችን ሥዕል ናት ብዙ ተአምራትን ስታደርግ ስላየ ወደአባ ዜና ማርቆስ በመሔድ ተምሮ ለማመን በቅቷል ከአባ ዜና ማርቆስ ትምህርተ ሃይማኖትን ተምሮ በምንኵስና ሕይወት መኖር ከጀመረ በኋላም ያችን ለማመን ያበቃችውን ገባሪተ ኃይል ሥዕል ሳይሳለም አይውልም ነበር፡፡
ከሥዕሏ ፊትም ሲቆም የሚያቀርበው እጅ መንሻ (መባዕ) ስለሌው ይጨነቅ ነበር በኋላ ግን ይህ ዘመነ ጽጌ ሲደርስ በየቀኑ ሃምሳ ሃምሳ የጽጌረዳ አበባ እየፈለገ እንደ ዘውድ እየጎነጎነ ለዚያች ምስለ ፍቁር ወልዳ ሥዕል ያቀዳጃት ነበር በጋው ሲወጣ የጽጌረዳው አበባ ስለደረቀበት ከሥዕሏ ተንበርክኮ እመቤቴ በየቀኑ የማመጣልሽ የጽጌረዳ አበባ ደረቀ ስለአበባው ፈንታ መልአኩ ተፈሥሒ ተፈሥሒ እያለ ያመሰገነሽን ምስጋና በአበባው ቁጥር ልክ ሃምሳ ሃምሳ ጊዜ እንዳመሰግንሽ ፍቀጅልኝ በማለት ተማጸነ ከዚህ በኋላ በየቀኑ ተፈሥሒ ፍሥሕት የሚለውን የመልአኩን ምስጋና በየቀኑ ሲያቀርብላት ምስጋናው እንደጽጌረዳ አበባ እየሆነ ከአንደበቱ ሲወጣ እመቤታችን አበባውን እየተቀበለች ስትታቀፈው ሰዎች እያዩ ያደንቁ እንደነበር ገድለ ዜና ማርቆስ ያስረዳል፡፡
እሱም በድርሰቱ እንዲህ ሲል ገልጾታል“አባዕኩ ለኪ ስብሐተ ተአምር ዘይሤለስ በበሃምሳ ህየንተ ጽጌያት ሃምሳ ለስዕልኪ አክሊለ ርእሳ” ለስዕልሽ ዘውድ ይሆን ዘንድ ሃምሳ የጽጌ ረዳ አበባ አቀርብልሽ ስለነበረው ፈንታ ሦስት ጊዜ ሃምሳ(መቶሃምሳ) የሚሆን ምስጋናን አቀረብኩልሽ በማለት፡፡ስለዚህ ዘመነ ጽጌ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ እግዚአብሔር ምድርን በአበባ ማስጌጡን ማሰባችን እንዳለ ሁኖ በተጨማሪ የእመቤታችን የስደቷን በዓል እናስብበታለን፡፡
                                           ስለምን ወደግብፅ ተሰደደ?   
ጌታችን ከመወለዱ በፊት ከጽንሰቱ እስከ ዳግም ምጽአቱ ድረስ ስለሚሠራው ሥራ አስቀድሞ በነቢያቱ እያደረ ትንቢት አናግሯል፡፡ መልአኩም ለዮሴፍ ብላቴናውን ሄሮድስ እንደሚገድለው ሲነግረው የሚሸሽበትን ቦታ ሳይቀር “ተንሥእ ንሣእ ሕፃነ ወእሞ ወሑር ውስተ ብሔረ ግብፅ” ተነስተህ እናቱንና ብላቴናውን ይዘህ ወደግብፅ ሽሽ በማለት ለስደቱ ግብፅን እንደመረጣት በትንቢቱ ተናግሯል(ማቴ፪፥፲፫) ከደቂቅ ነቢያት አንዱ ሆሤዕም ጌታችን ወደግብፅ እንደሚሰደድ “እምግብፅ ጸዋእክዎ ለወልድየ ልጄን ወደግብፅ ጠራሁት” ሲል ልዑለ ቃል ኢሳይያስ ደግሞ “ወይወርድ እግዚእነ ውስተ ምድረ ግብፅ እንዘ ይጼዐን ዲበ ደመና ቀሊል፤ጌታችን በፈጣን ደመና (በእመቤታችን ጀርባ) ተጭኖ ወደግብፅ ይወርዳል በማለት ተናግሯል (ሆሴ፲፩፥፩ ኢሳ ፲፱፥፩)ከሌሎች ሀገሮች ለስደቱ ግብፅ የተመረጠችበት ምክንያቱ ብዙ ቢሆንም ጥቂቶቹን እንመለከታለን፡፡
፩.ለፍቅሩ ስለሚሳሱለት፤ ጌታችን ወደግብፅ የተሰደደበት ምክንያት ግብፃውያን ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ጌታችን ከምንም በላይ ለፍቅሩ ይሳሱለት ስለነበረ ነው፡፡ይህንም ወደ ግብፅና ወደ ኢትዮጵያ በተሰደደ ጊዜ ግብፃውያንና ኢትዮጵያውያን እንዴት አክብረው እንደተቀበሉትና እንደሳሱለት በነገረ ማርያም የተጻፈው ታረክ ጥሩ ማስረጃ ነው ምንም ሰይጣን ያደረባቸው እነ ኮቴባን የመሰሉ አንዳንድ ክፉ ሰዎች ቢያጋጥሟቸውም ብዙዎቹ ደግሞ ለፍቅሩ በመሳሳት“ደም ግባቱ ከሰው ልጆች ሁሉ ያምራል”ተብሎ የተነገረለትን መልኩን በማየት ብቻ ለማመን የበቁ ደጋጎች ነበሩ እንኳን ቤት መስርተው በዓለም የሚኖሩት በበረሃ ውስጥ የሚኖሩ ሽፍታዎችም ለጌታችን ያሳዩት ርኅራኄና ፍቅር የተለየ ነበር፡፡ሕፃኑ ኢየሱስ ክርስቶስና እመቤታችን ዮሴፍና ሰሎሜ ኢየሩሳሌምን ለቀው ወደ ግብፅ ሲሰደዱ ግብፃዊው ጥጦስና አይሁዳዊ ዳክርስ ሁለት ወንበዴዎች በረሃ ውስጥ አግኝተዋቸው ነበር እስራኤላዊዉ ዳክርስ ልብሳቸውን ለመግፈፍ ሲፋጠን ግብፃዊዉ ጥጦስ ግን በልቡናው ርኅራኄ አድሮበት ለፍቅሩ በመሳሳት እነዚህ ሰዎች የቤተ መንግሥት ሰዎች ናቸው አሳዘኑኝ ወደ ዚህ ቦታ የመጡት ያለ ምክንያት አይሆንምና አንቀማቸው እንተውላቸው በማለት ለጌታ ያለውን ፍቅርና ርኅራኄ ገልጧል
ወደ ኢትዮጵያም በመጡበት ወራት ቤታቸውን እየለቀቁ ያስተናግዷቸው እንደ ነበር ድርሳነ ዑራኤል በሰፊው ይናገራል እመቤታችንም የኢትዮጵያ ሰዎች ባሳዩአት ፍቅር ስትደሰት ጌታችን የዐሥራት ሀገር ትሁንሽ ብሎ ሀገሪቱን ለእመቤታችን የሰጣት በወቅቱ የነበሩት ኢትዮጵያውያን ባሳዩት ደግነትና ርኅራኄ ነው፡፡ደጉ አባት አብርሃም እንግዳ በመቀበሉና ደግ በመሆኑ ሥላሴ ከቤቱ እንደ ገቡለት ሎጥም እንግዳ በመቀበል መላእክት ወደ ቤቱ ገብተው ሰዶምና ገሞራ ሲጠፉ ከጥፋት እንደታደጉት ጌታችን አባቶቻችን ባደረጉት ደግነት ኢትዮጵያ በእመቤታችን ምልጃ ሊጠብቃት ስለፈለገ የዐሥራት ሀገር አድርጎ ሰጣት ምን ጊዜም ሊምረው የወደደውን ሰው የእመቤታችን ፍቅር ያሳድርበታልና እመቤታችን እንድንወድ አድርጎ በአማላጅነቷ እንድንጠበቅ ፈቀደልን ጌታችን ወደ ግብፅና ወደ ኢትዮጵያ የተሰደደበት ምክንያት ለፍቅሩ ይሳሱለት ለነበሩት ኢትዮጵያና ግብፅ በፍቅር ለመገለጽ ሲሆን በተጨማሪም ገዳማተ ግብፅንና ገዳማተ ኢትዮጵያንም ለመባረክ ጭምር ነው፡፡በግብፅና በኢትዮጵያ ያሉ ታላላቅ ገዳማት የተባረኩት በስደቱ ወራት ነውና፡፡
ኪዳነ መልከ ጼዴቅን ለመፈጸም ነው፤መልከ ጼዴቅ ከዘመዶቹ ተለይቶ በምናኔ ሲኖር በሚያቀርበው መሥዋዕት በሚጸልየው ጸሎት በሥጋ ዘመዶቹ የሆኑትንና የማይዘመዱትን እንዲምርለት እግዚአብሔርን ይለምነው ነበር እንዲህ እያለ አቤቱ ለዲያብሎስ ከመገዛት ለአንተ ወደ መገዛት መልሰኸኛልና ከሀገሬም አውጥተህ አንተን ወደማመልክበት ቦታ አምጥተኸኛልና በደሌንም ይቅር ብለህልኛልና አመሰግንሃለሁ ነገር ግን እኔን ይቅር እንዳልከኝ ዘመዶቼንም ማርልኝ፡፡እግዚአብሔርም ልመናውን ተቀብሎ እንዲህ ሲል ድምፁን አሰምቶታል ልጄን ወደ ግብፅ በጠራሁት ጊዜ ዘመዶችህን እምርልሃለሁ ብሎ ቃለ ኪዳን ገብቶለት ነበር ዘመኑ ሲደርስ የተናገረውን የማያስቀር እግዚአብሔር የገባለትን ቃለ ኪዳን ለመፈጸም ወደግብፅ ተሰደደለት (ተረፈ ቄርሎስ ፳፭፥፩—፱) ኖኅ ከጥፋት ውኃ በኋላ መልአከ እግዚአብሔርን ከመካከላቸው እንደ ዳኛ አስቀምጦ ለሦስቱ ልጆቹ ለሴም ለካም ለያፌት ይህን ዓለም ቀኝ ቀኙን ለሴም መሀሉን ለያፌት ግራ ግራውን ለካም አውርሷቸዋል መልከ ጼዴቅ ትውልዱ ከካም ወገን ስለሆነ ምንም ዘመዶቼን ማርልኝ ብሎ የጸለየ ለሁሉም ዘመዶቹ ቢሆንም የአባቱ ወገኖች የካም ዘሮች ናቸውና ጌታ ወገኖቹን ሊምርለት ቃል ኪዳኑን ሊፈጽምለት ወደግብፅ ተሰዷል
.አጋንንትን ከግብፅና ከሰው ልቡና አስወጥቶ ለመስደድ ነው
ጌታ ገና ከመወለዱ በፊት ለልደቱ ሃያ አራት ቀን ሲቀረው መካነ ልደቱ ቤተ ልሔምን በመላእክት አስጠብቋት ነበር፡፡በዚህ ጊዜም አጋንንት በመላእክት ረቂቅ ጦር እየተወጉ ኢየሩሳሌምን ለቀው ሲወጡ የተሰደዱት ወደ ግብፅ ነበር አጋንንት በውስጣቸው አድርው ይመለኩባቸው የነበሩ ጣዖታትም ተሰባብረው ጠፍተዋል ይህንንም ጌታ ወደ ግብፅ በተሰደደ ጊዜ ራሳቸው አጋንንት በኢየሩሳሌም ማደሪያ እንዳሳጣኸን በዚህም ልታሳድደን መጣህን ብለው እንደ መሰከሩ በነገረ ማርያም ተጽፏል ጌታ ወደግብፅ የተሰደደበት ሦስተኛው ምክንያት እነዚህ አጋንንት ማደሪያ ካደረጓቸው የሰው ልቡናናና ከጣዖቱ አስወጥቶ በመስደድ አጋንንትን ለማሳደድ ነው፡፡ ይህንም ቴዎዶጦስ የተባለው ሊቅ ጌታ ተሰደደ ሲባል ብትሰማ ፍጡር ነው ብለህ አትጠራጠር ፈርቶ ሸሸም አትበል የጌታ መሰደድ ዲያብሎስን ከሰው ልቡና አስወጥቶ ለማሳደድ እንደሆነ እመን እንጅ ብሎ የተሰደደ ዲያብሎስን ለማሳደድ መሆኑን ገልጧል (ተረፈ ቄር፲፥፭)ይህ ሊቅ ጌታ የተሰደደው ዲያብሎስን ለማሳደድ ብቻ ሳይሆን ሰው መሆኑን ለሚጠራጠሩ፣ምትሐት ነው ለሚሉትም በትክክል ሰው መሆኑን ለማስረዳት እንደ ተሰደደ በዚሁ ምዕራፍና ቁጥር ይገልጻል ሰው ባይሆን ኑሮ አይሰደድም ነበር ፡፡
.አዳም ከዚህ ዓለም አፍአ በምትሆን ከገነት ተሰዶ ነበርና ለመካስ
ጌታችን በዕለተ ልደቱ የበለስ ቅጠል የለበሰ አህዮችና ላሞች እስኪያሟሙቁት ድረስ የተበረደ አዳም ከገነት ሲወጣ የበለስ ቅጠል ስለለበሰ ከልብሰ ብርሃን በመገፈፉ ስለተበረደ አዳም የተቀበለውን መከራ ተቀብሎ ለመካስ ነው፡፡ገና በሁለት ዓመቱ ከኢየሩሳሌም ወደግብፅ የተሰደደውም ከዚያው ሁኖ መዳን ተስኖት ሳይሆን አዳም ዕፀ በለስን በልቶ ከገነት እንደ ተሰደደ እሱም ከኢየሩሳሌም ወደ ምድረ ግብፅ ተሰዶ አዳም የተቀበለውን መከራ ተቀብሎ ለመካስ ነው፡፡አዳም ከገነት ወደ ማያውቀው ወደዚህ ዓለም ሲሰደድ ብዙ ፍዳና መከራ አግኝቶታል ፡ከአንዱ ቦታ ወደ አንዱ ቦታ በሚያደርገው እንቅስቃሴ እሾሁ ሲወጋው እንቅፋቱ ሲመታው ይህ ሁሉ የደረሰበት ከፈጣሪዉ ትእዛዝ በመውጣቱ መሆኑን ሲያስብ ዕንባው ከዓይኑ ያለማቋረጥ እንደምንጭ ውኃ ይፈስ ነበር፡፡
በገነት ሳለ የሚበላውና የሚጠጣው ከሰውነቱ ጋር ተዋሕዶ ይቀር ነበር እንጅ ወደ ኀሠርነት ስለማይለወጥ በልቶ ጠጥቶ መጨነቅ ሆድ ቁርጠት በልቶ መታመም በቁንጣን መሰቃየት አልነበረበትም ከገነት ከወጣ በኋላ ግን ይህ ሁሉ መከራ በርሱ ላይ መጥቶበታል ይህን ሁሉ መከራ ስለተቀበለ አዳም ወደዚህ ዓለም ሲሰደድ የተቀበለውን መከራ ተቀብሎ ሊክሰው ስለወደደ ወደ ግብፅ ተሰደደለት እንደተበረደ ተበረደለት በዕፀ በለስ ምክንያት ከገነት እንደወጣ በዕፅ ተሰቅሎ ያጣው ክብሩንና የክብር ቦታውን ገነትን መለሰለት
፭ ለሰማዕታት ስደትን ለመባረክ ፤ሰማዕትነት እሳትና ስለት ብቻ አይደለም ሀገርን ጥሎ መሰደድም ሰማዕትነት ነው፡፡ በመሆኑም ለሰማዕታት ስደትን ለመባረክ የማትችሉት መከራ ቢመጣባችሁ ተሰደዱ ለማለት ወደ ግብፅ ተሰደደ ስደት ከሰማዕትነት ገብቶ የተቆጠረበት ምክንያት መከራው በሰይፍ ተቆርጦ በስለት ተቀልቶ ከመሞት በላይ ስለሆነ ነው፡፡ከመከራ ሁሉ ከባዱ መከራም ደም ሳይፈስ በየጊዜው የሚፈጸመው የሰማዕትነት ተጋድሎ ነው በሰይፍ ተቀልቶ እሳት ውስጥ ገብቶ መሞት ቀላል ነው ባይባልም አስፈሪ ቢሆንም በስደት ልዩ ልዩ መከራ ከመቀበልና በየጊዜው ከመፈተን ግን የተሻለ ነው ሰይፍ የሚያስፈራው ለተወሰነ ደቂቃ ነው ስደት ግን በየጊዜው ከሰይፍ በላይ በሚያም መከራ መቆረጥና መሰቃየት ነው እመቤታችን በስደቷ ጊዜ ልጇ እንዳይሞትባት ከሰው ለመሰወር በበረሃው ስትሔድ ግሩማን አራዊት ያስደነግጧት ነበር ሰው ወዳለበት መንደር ስትሔድ ሰዎች ይጣሏታል፡፡
በዚያ ላይ ደግሞ ቀን ሐሩረ ፀሐዩ ሌሊት ቁረ ሌሊቱ እየተፈራረቀባት እሾሁ እየወጋት እንቅፋቱ እየመታት መውጫና መግቢያው በማይታወቅ በረሓ ውስጥ ገብቶ መሰቃየቱ የመንገዱ መጥፋት በዚያ አሰልችና አድካሚ ጉዞ ውስጥ የልጇ በውኃ ጥም መቃጠልና ማልቀስ ለእመቤታችን ሌላው ሰማዕትነት ነበር ይህን ሁሉ መከራ መቀበሏ ግን ሰማዕታትን በስደትና በልዩ ልዩ መከራ ሲሰቃዩ መከራውን እንዲችሉ ያደርጋቸዋል፡፡ለምን ይህ ሁሉ መከራ አገኘን ብሎ ተስፋ እንዳይቆርጡ ተስፋ ይሆናቸዋል ስለዚህ ለምን ይህ ሁሉ መከራ ደረሰብን ብለው ተስፋ እንዳይቆርጡ እመቤታችን ከተወደደ ልጇ ጋር ስደትን ባርካ ሰጠቻቸው እሷን መሠረት አብነት በማድረግም ብዙ ቅዱሳን ለሃይማኖታቸው ለቤተ ክርስቲያናቸው በስደትና በስለት መከራ ተቀበሉ ዋሻ ለዋሻ በረሓ ለበረሓ ተንከራተቱ ግን ተስፋ አልቆረጡም እመቤታችን መጽናኛ ሁናቸዋለችና ስለዚህ እመቤታችን በስለት ከሚፈጸመው መከራ ውጭ ያልተቀበለችው መከራ ስለሌለ እሞሙ ለሰማዕት የሰማዕታት እናታቸው እየተባለች ትመሰገናለች(ቅዳሴ ማርያም)
የቅዱሳንን ገድልና መከራ የሚናገረው ስንክሳር የቤተ ክርስቲያናችን መጽሐፍም ስደት እሳትና ስለት ብቻ አለመሆኑን እየተሰደዱ እየታሠሩ እየተገረፉ መከራ የሚቀበሉትን ቅዱሳን ሰማዕት ዘእንበለ ደም እያለ ይጠራቸዋል ሰማዕት ዘእንበለ ደም ማለትም ደማቸው ሳይፈስ ሰማዕትነትን የተቀበሉ ማለት ነው፡፡የእነዚህ ሰማዕታት ሰማዕትነት አንድ ጊዜ በማይገድል በየጊዜው በሚደርስ መከራ መሰቃየት ነውና፡፡
        በስደቷ ጊዜ ያገኛት መከራ
እመቤታችን ከተወደደ ልጇ ጋር በተሰደደችበት ጊዜ ልዩ ልዩ መከራ አግኝቷታል፡፡መከራውም ለእመቤታችን ኀዘን ጭንቅ ቢሆንም ለእኛ ግን ደስታና ድኅነት ነበር ምክንያቱም ከእመቤታችን በኋላ የነበሩ አባቶቻችንና የነርእሱ ልጆች የሆንነው እኛ ዛሬ ላይ ስደቷን መከራዋን እያሰብን የቻልን ሰውነታችን በጾም እያደከምን ያልቻልን ማኅሌት እየቆምን ለርሷና ለልጇ የምስጋና እጅ መንሻ እያቀረብን በስደቷ ወራት የደረሰባትን መከራ እያዘከርን እንድታማልደን እንማጸንበታለን በረከትም እናገኝበታለን፡፡ አባ ሕርያቆስ በቅዳሴ ማርያም ድርሰቱ ላይ “አዘክሪ ድንግል ንግደቶ ዘምስሌኪ እንዘ ትጐይዪ ምስሌሁ እሀገር ለሀገር በመዋዕለ ሄሮድስ ርጉም አዘክሪ ድንግል አንብዐ መሪረ ዘውኅዘ እምአዕይንትኪ ወወረደ ዲበ ገጸ ፍቁር ወልድኪ አዘክሪ ድንግል ረኀበ ወጽምዐ ምንዳቤ ወኀዘነ ወኵሎ ዐፀባ ዘበጽሐኪ ምስሌሁ፤ርጉም ሄሮድስ በነገሠበት ወራት ከአንቺ ጋር ከአንዱ ሀገር ወደ አንዱ ሀገር የተሰደደውን መሰደድ አሳስቢልን በአይኖችሽና በልጅሽ ፊት የወረደውን መሪር ዕንባ አሳስቢልን ረሀቡን ጥሙን ችግሩንና ኀዘኑን ያገኘሽንም ልዩ ልዩ መከራ አሳስቢልን (ቅዳሴ ማርያም)በማለት እመቤታችን ሔሮድስ በነገሠበት ወራት ከአንዱ ሀገር ወደሌላው ሀገር መሰደዷን፣ ከዓይኗ የፈሰሰውንና በልጇ ፊት የወረደውን ዕንባ አማላጅ አድርጋ እንድታሳስብልን ይናገራል ይህንም ቃል ቅዳሴ ማርያም በተቀደሰበት ቀን ቤተ ክርስቲያናችን ሁልጊዜ ካህናቱ ሥጋውን ደሙን አቀብለው ከተመለሱ በኋላ ትጸልየዋለች እኛን ኀጥአንንም ታማልድበታለች፡፡
እመቤታችን በተሰደደችበት ወራት ካጋጠማት ጭንቅ ጭንቅ መከራ ሁሉ የሚበልጠው በልጇ ላይ የሚመጣው መከራ ነበር ምክንያቱም ሀገር ጥላ የተሰደደችው ተወዳጁን ልጇን ከሞት ለማዳን ነውና፡፡ሄሮድስ አራት ወታደሮችን ከነሠራዊታቸው በሽልማት ሸልሞ እመቤታችን ከነልጇ ይዘው ከመጡ የበለጠ ሹመትና ሽልማት እንደሚጠብቃቸው አብስሮ ልኳቸው ነበር፡፡
የዮሴፍ ልጅ ዮሳ ይህንን ምስጢር ለአባቱ ለዮሴፍና ለእመቤታችን እንዲሁም ለሰሎሜ ለመንገር ከነበረው ኃይል ላይ የአንበሳ ኃይል ተጨምሮለት በፍጥነት ሲጓዝ እያለ የመልካም ነገር ጠላት የሆነው ሰይጣን መንገድ ላይ ጠብቆ ወዴት እንደሚሔድ ጠየቀው ዮሳም በየዋህነት የሚሮጥበትን ጉዳይ ሳይደብቅ ዘርዝሮ ነገረው ሰይጣንም የሄሮድስ ሠራዊት ቀድመው መሔዳቸውን በሔዱበት ፍጥነት ካገኟቸው እንደሚገድሏቸው ዮሳም በከንቱ እንዳይደክም ያዘነ በሚመስል ድምፅ እንዲመለስ ነገረው ዮሳ ግን ሐሳቡን ሳይቀበል ከሞቱም እቀብራቸዋለሁ በሕይወት ካሉም የሆነውንና የታሰበውን ነግሬ እንዲሸሹ አደርጋለሁ ብሎ መገስገስ ጀመረ ኃይል ከእግዚአብሔር ተጨምሮለታልና፡፡
ዮሳ እየሮጠ ሲሔድ መንገድ ላይ አገኛቸውና ገና ከመድረሱ እመቤታችን ያስደነገጠ ሕሊናዋን የረበሸ ምርር ብላም እንድታለቅስ የሚያደርግ አሰቃቂ ዜናን ነገራት እመቤታችንም የዮሳን ቃል ሰምታ ከአንዱ ሀገር ወደ ሌላኛው ሀገር የተሰደድኩት ከሞት ላላድንህ ነውን? ልጄ አንተን ሲገሉህ ከማይ እኔ አስቀድሜ ልሙት በማለት ስታለቅስ ሕፃኑ ኢየሱስ ክርስቶስ በእጁ ዕንባዎቿን በማበስ እንደማይሞት ከነገራት በኋላ ፊቱን ወደ ዮሳ መልሶ ዮሳ ዕሡይ ምጽአትከ (አመጣጥህ ዋጋ የሚያሰጥ መልካም) ነበር ነገር ግን እናቴን አስደንግጠሃታልና በዕለተ ምጽአት አስነሥቼ ዋጋህን እስከሰጥህ ድረስ ይህችን ደንጋይ ተተንተርሰህ ዕረፍ ብሎት ዐርፋል፡፡
እንግዲህ እመቤታችን በስደቷ ወራት ውኃ በመጠማት በመራብ እሾሁ እየወጋት እንቅፋቱ እየመታት ቀን የበረሓው ሐሩር እያቃጠላት ሌሊት ደግሞ ብርዱ እያሳቃያት ትጓዝ ስለነበር ያገኛትን መከራ በቃላት ገልጾ መጨረስ አይቻልም በተለይ ሰው ስታይ ልጇን የሚገድሉባት ስለሚመስላት በጣም ትጨነቅም ታለቅስም ነበር፡፡
አባ ሕርያቆስም በስደትሽ ወራት ያገኘሽን ልዩ ልዩ መከራ ከልጅሽ ዘንድ አሳስቢልን ያለው ያገኛትን መከራ አስባ እኛንም ከአስፈሪ ፈተና እንድታወጣን ነው አባቶችም እመቤታችን መከራዋን እያነሡ ካለቀሱና ከለመኗት ፈጥና እንደምትሰማ በሕይወታቸው ካገኙት ተሞክሮ ተነሥተው ይናገራሉ፡፡ስለዚህ እኛም በወርኀ ጽጌ ስደቷን ስናስብ የራሳችንንም የሀገራችንንም ችግር አብረን ልናስብ ይገባል፡፡በተለይ በሀገር የሚመጣ ችግር ለሁላችንም የሚተርፍ ስለሆነ እመቤታችን የዐሥራት ሀገሯን በአማላጅነቷ እንድትጠብቃት ሁላችንም የቻልነውን ያህል በወርኀ ጽጌ ተግተን ልንጸልይ ማኅሌት ልንቆም በጸሎት ልንበረታ ይገባል አምላካችን እግዚአብሔር የሀገራችን ጥፋት አያሳየን አሜን፡፡
ምንጭ፤ሐመር መጽሔት ፳፮ኛዓመት ቊ ፮ ጥቅምት ፳፻፲ወ፩ ዓ.ም

  Ethiopia is our great home built by the bones of our ancestors!!! According to our fathers, our mother, our wife, our sister ……..it is al...