በመ/ር ምስጢረ ሥላሴ ማናየ
መጋቢት ፲፮ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስያሜ የዐቢይ ጾም
ስድስተኛው እሑድ ወይም ሳምንት ‹ገብር ኄር› ይባላል፡፡ ሰያሜውን የሰጠውም ኢትዮጵያዊ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ነው፡፡
ከአምስቱ መጻሕፍቶቹ አንዱ በኾነው ጾመ ድጓ መጽሐፍ ሳምንቱን የዐቢይ ጾም ሳምንታት ስያሜዎች ከነሥርዓተ ማኅሌቱ
አዘጋጅቷል፡፡ ስለዚህ በስድስተኛው የዐቢይ ጾም ሳምንት ከዋዜማው ቅዳሜ ጀምሮ በቤተ ክርስቲያን የሚዘመረው ዝማሬ፣
የሚሰበከው ስብከት፣ የሚሰጠው ትምህርት ገብር ኄርን የሚያወሳ ነው ማለት ስለ ታማኝ አገልጋይ የሚያስረዳ ነው፡፡
በማቴዎስ ወንጌል ፳፭፥፲፬-፳፭ የተገለጸውና በዕለቱ የሚነበበው ወንጌል የሚነግረንም ይህንኑ ትምህርት ነው፡፡
አንድ ባዕለ ጸጋ ሰው ባሪያዎችን ጠርቶ ለአንዱ አምስት መክሊት
ሰጠው፣ ሁለት መክሊት የሰጠውም አለ፣ አንድ መክሊትም የሰጠው አለ፡፡ ከዚህ በኋላ ወደሩቅ አገር ሔደ፡፡ አምስት
መክሊት የተቀበለውም ወጥቶ ወርዶ ሌላ አምስት አትርፎ ዐሥር አደረገ፡፡ ሁለት የተቀበለውም አትርፎ አራት አደረገ፡፡
አንድ የተቀበለው ግን መሬቱን ቆፍሮ በሻሽ ጠቅልሎ የጌታውን መክሊት ቀበራት፡፡ ከብዙ ጊዜ በኋላ ጌታቸው መጥቶ
ተቆጣጠራቸው፡፡ አምስት መክሊት የተቀበለው ቀርቦ ‹‹ጌታዬ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር እነሆ አምስት አተረፍኩ›› አለው፡፡ ‹‹ገብር ኄር ወምዕመን ዘበውሁድ ምእምነ ኮንከ ዲበ ብዙህ እሰይመከ ባእ ውስተ ፍሥሐሁ ለእግዚእከ፤ አንተ ታማኝ ባሪያ! በጥቂቱ ታምነሃል፤ በብዙ እሾምሃለሁ፡፡ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ!›› አለው፡፡ ሁለት የተቀበለውም ቀርቦ ‹‹ጌታዬ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር እነሆ ወጥቼ ወርጄ ሌላ ሁለት አትርፌ አራት አድርጌአለሁ፤›› ብሎ መክሊቱን አቀረበ፡፡ ጌታውም፡- ‹‹አንተ ታማኝ በጎ አገልጋይ በጥቂቱ ታምነሃል፤ በብዙ እሾምሃለሁ፡፡ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ!›› አለው፡፡
አንድ መክሊት የተቀበለው ግን ‹‹ጌታዬ፣ አንተ ክፉና ጨካኝ፤ ካልዘራህበት የምታጭድ፤ ካልበተንህበት የምትሰበስብ፤ እንደ ኾንክ ስለ አወቅሁ መሬቱን ቆፍሬ ቀበርኋት እነኋት መክሊትህ›› አለው፡፡ ‹‹አንተ ሰነፍ ባሪያ! መክሊቴን በጊዜ ልትሰጠኝ በተገባህ ነበር፡፡ እኔም ወጥቶ ወርዶ ለሚያተርፍ በሰጠሁት ነበር፤›› አለና ‹‹ኑ፤ የዚህን ሐኬተኛ መክሊት ውሰዱና ዐሥር መክሊት ላለው ስጡት፡፡ ‹ላለው ይሰጡታል ይጨመርለታል ለሌለው ግን ያለውን ይቀሙታል›፡፡ ንዑ ይህን ሰነፍና ሐኬተኛ ባርያ እጅ እግሩን አሥራችሁ ጽኑ ጨለማ ወደ አለበት ውሰዱት! ጩኸትና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት ጨምሩት!›› የሚል ፍርድ ወሰነበት፡፡
ባዕለ ጸጋ የተባለው ጌታ ነው፡፡ መክሊት የተባለው ልዩ ልዩ
የአገልግሎት ጸጋ ነው፡፡ ያተረፉት በሚገባ በታማኝነት ያገለገሉ ቅዱሳን ሰዎች ናቸው መክሊቱን የቀበረው ደግሞ
በታማኝነት በተሰጠው ጸጋ ማገልገል ሲገባው ያላገለገለ ነው፡፡ ጌታቸው ሊቆጣጠራቸው መጣ ማለት ጌታችን በዕለተ
ምጽአት ለዅሉም በሠራው ምግባር መጠን ዋጋ ለመስጠት እንደሚመጣ ያሳየናል፡፡ ያገለገሉትን ‹‹ወደ ጌታህ ደስታ ግባ!›› አላቸው ማለት ታማኝ አገልጋዮች መንግሥተ ሰማያትን ይወርሳሉና፡፡ ሰነፉ አገልጋይ ወደ ጨለማና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት ቦታ መወርወሩም ኀጥአን ወደ ሲኦል መግባታቸውን የሚያሳይ ነው፡፡
ከላይ ያነሳነው የቅዱስ ወንጌል ቃል፡- ‹‹ታማኝ አገልጋይ ማነው?››
ይላል፡፡ ይህ እያንዳንዱ በአርአያ እግዚአብሔር የተፈጠረ የሰው ልጅ ጥያቄ ነው፡፡ ለዚህ አምላካዊ ጥያቄ ምላሽ
መስጠት ከሰው ልጆች ይጠበቃል፡፡ ከዚህ ቀጥለን በመጽሐፍ ቅዱስ ታሪካቸው ከተመዘገበላቸው ታማኝ አገልጋዮች መካከል
ሦስቱን ጠቅሰን ከእነርሱ ሕይወት እንድንማር የሚያነሣሣ መጠነኛ ትምህርት እናቀርባለን፤
ሙሴ
ሊቀ ነቢያት ሙሴ ታማኝ አገልጋይ መኾኑን ቅዱሳት መጻሕፍት ይመሰክራሉ፤ ‹‹በመካከላችሁ ነቢይ ቢኖር እኔ እግዚአብሔር በራእይ እገለጥለታለሁ ወይም በሕልም አናግረዋለሁ፡፡ ባሪያዬ ሙሴ ግን እንዲህ አይደለም እርሱ በቤቴ ዅሉ የታመነ ነው፤››
እንዲል (ዘኍ.፲፪፥፮)፡፡ ይህ የፍጡር ቃል ሳይኾን በፈጣሪው የተሰጠ ምስክርነት ነው፡፡ በውኑ በዘመናችን እንኳን
ፈጣሪ ፍጡራን ታማኝነቱን የሚመሰክሩለት አጋልጋይ ይኖር ይኾን? እንጃ! የሙሴን ታማኝ አገልጋይነት በረኃ፣ ስደት፣
መከራ፣ የፈርዖን ግርማ እና ቁጣ አልበገረውም፡፡ ዐርባ ዓመት ስለ ወንድሞቹ በመሰደድ ዐርባ ዓመት ደግሞ
የተሰደደላቸው ወንድሞቹን በመምራት፣ ባሕር በመክፈል፣ ጠላት በመግደል፣ መና በማውረድ፣ ደመና በመጋረድ ውኃ ከዓለት
አፍልቆ በማጠጣት መከራውን ከወገኖቹ ጋር በመቀበል የቀኑን ኃሩር፣ የሌሊቱን ቁር (ብርድ) ታግሦ በታማኝነት
አገልግሏል፡፡ ታማኝነቱም እስከ ሞት ድረስ ነበር፡፡
‹‹ሙሴም ወደ እግዚብሔር ተመልሶ ‹ወዮ እኒህ ሕዝብ ታላቅ ኃጢአት ሠርተዋል፡፡ ለራሳቸውም የወርቅ አማልክት አድርገዋል፡፡ አሁን ይህን ኀጢአታቸውን ይቅር በላቸው፤ ያለዚያ ግን ከጻፍከው መጽሐፍ እባክህ ደምስሰኝ? ከባለሟልነትህ አውጣኝ?›› ተብሎ ተጽፏል (ዘፀ.፴፪፥፴፩)፡፡ ታማኝ አገልጋይ የሚባለው እንደ ሙሴ ‹‹እኔ ልሙት ሌሎች ይዳኑ›› የሚል ሰው ነው፡፡ አሁን የምናየው ግን ፈጽሞ ከዚህ የተለየ ነው፡፡ ‹‹ሰዎች ይሙቱ፤ እኔ ልኑር፡፡ ሰዎች ጦም ይደሩ፤ እኔ ልብላ፡፡ ሰዎች ይራቆቱ፤ እኔ ልልበስ፡፡ ሰዎች ይዘኑ፤ እኔ ልደሰት›› ነው፡፡ ይህም ታማኝ አገልጋይ ያለ መኾን መገለጫ ነው፡፡ ታማኝ አገልጋይ ለሚያገለግላቸው ሰዎች ጥቅም ቅድሚያ የሚሰጥ እንጂ የራሱን ጥቅም የሚያስቀድም አይደለም፡፡
ዛሬ በዓለማችን የምንመለከተው ድርጊት ግን ‹‹ጩኸት ለአሞራ መብል ለጅግራ››
የሚባለውን ዓይነት ነው፡፡ በታማኝ አገልጋዮች ድካም የሚሸለሙ፤ ታማኝ አገልጋዮች በሠሩት ሪፖርት የሚያቀርቡ፤
ባልሠሩት ሥራ የሚወደሱ፤ ከጥቅሙ እንጂ ከድካሙ መካፈል የማይሹ ጥቂቶች አይደሉም፡፡ እንቅፋት የሚመታው እግርን
ነው፡፡ አክሊል የሚቀዳጀው ግን ራስ ነው፡፡ ታማኝ አገልጋይ ማለት እንደራስ አክሊል ዘውድ የሚጸፋ ብቻ ሳይኾን
እንደ እግር እንቅፋቱን፣ እሾኹን፣ ውጣ ውረዱን፣ መከራውንና ድካሙን የሚቀበል ነው፡፡ በጥቅም ጊዜ ለራሱ በአካፋ
የሚዝቅ፤ ሌሎች በጭልፋ የሚቆነጥር አይደለም፡፡ ሙሴ ባሕር የከፈለው፣ መና ያወረደው ደመና የጋረደው ውኃ ያፈለቀው
ለራሱ አልነበረም፤ ለሚመራቸው ሕዝብ ነበር እንጂ፡፡ ታማኝ አገልጋይ ያሰኘውም ይኸው ነው፡፡ በዚህ ከብሮበታል፤
ተመስግኖበታልም፡፡
ዳዊት
ነቢዩ ዳዊት ዘመነ መሳፍንት አልፎ ዘመነ ነገሥት ሲተካ
እስራኤልን በንጉሥነት እንዲመራ እግዚአብሔር ከበግ ጥበቃ የመረጠው ንጉሥ ነው፡፡ እርሱም በተሰጠው ሥልጣን ሳይታበይ
በታማኝነት ሕዝበ እስራኤልን መርቷል፡፡ እግዚአብሔር ለሙሴ እንደ መሰከረው ዅሉ ስለ ለዳዊትም መስክሮለታል፡፡ ‹‹እግዚአብሔር እንደ ልቡ የኾነ ሰው መርጧልና … የዘይቱን ቀንድ ሞልተህ በልጆቹ መካከል ለእኔ ንጉሥ አዘጋጅቻለሁና ወደ እሴይ ወደ ቤተ ልሔም እልክሃለሁ፤›› ተብሎ እንደ ተጻፈ (፩ሳሙ. ፲፫፥፲፫፤ ፲፮፥፪)፡፡
በመዝሙረ ዳዊትም ‹‹ወረከብክዎ ለዳዊት ገብርየ ወቀባዕክዎ ቅብዐ ቅዱስ፤ ባሪያዬ ዳዊትን አገኘሁት የተቀደሰ ዘይትንም ቀባሁት›› ተብሎ ተነግሮለታል (መዝ. ፹፰፥፳)፡፡ ይህንንም አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በመጽሐፈ ሰዓታት ድርሰቱ፡- ‹‹ረከብክዎ ለዳዊት ገብርየ ብእሴ ምእመነ ዘከመ ልብየ፤ አገልጋዬ ዳዊትን እንደ ልቤ የታመነ ሰውን ኾኖ አገኘሁት››
ሲል ተርጕሞታል፡፡ ንጉሥ ዳዊት ከመንገሡ በፊት የተገኘው በታማኝነት ነበር፡፡ ከነገሠ በኋላም ታማኝ ነበር፡፡
አሁን በዚህ ዓለም የምንኖር እኛ ግን በድኅነት ታማኝ እንኾንና ሀብት፣ ሹመት፣ ሥልጣን ሲመጣ ታማኝነትን እናጣለን፤
እንዲያውም ታማኝነትን እንንቀዋለን፡፡ መስረቅ ጀግንነት ይመስለናል፡፡ መዋሸት ሥልጣኔ ይኾንልናል፡፡
ዳዊት ሳይሾም በጎቹን በመጠበቅ ታማኝ ነበር፡፡ በጎቹን የሚነጥቅ ተኩላ አንበሳ ቢመጣ በኋላው ተከትሎ ነብሩን በጡጫ፣ አንበሳውን በእርግጫ ብሎ በጎቹን ያስጥል ነበር፡፡ ‹‹እኔ ባሪያህ የአባቴን በጎች ስጠብቅ አንበሳ ወይም ድብ ይመጣ ነበር፡፡ ከመንጋውም ጠቦት ይወስድ ነበር፡፡ በኋላውም እከተለውና እመታው ነበር፤ ከአፉም አስጥለው ነበር፡፡ በተነሣብኝም ጊዜ ጉሮሮውን አንቄ እመታውና እገድለው ነበር፡፡ ይህም ፍልስጥኤማዊ ከነዚያ እንደ አንዱ ይኾናል፤ እንግዲህ እገድለው ዘንድ፤ ከእስራኤል ተግዳሮትን አስወግድ ዘንድ ዛሬ አልሔድምን? የሕያው አምላክ ጭፍሮችን ይገዳደር ዘንድ ይህ ቆላፍ ምንድን ነው? ከአንበሳና ከድብ ያስጣለኝ እግዚአብሔር ከዚህ ያልተገረዘ ፍልስጥኤማዊ እጅ ያስጥለኛል!›› በማለት እርሱ እንደ ተናገረው (፩ኛሳሙ.፲፯፥፴፬)፡፡
ዛሬም ቢኾን በእስራኤል ዘነፍስ በምእመናን ላይ የሚገዳደሩ ብዙ
ፍልስኤማውያን ተሰልፈዋል፡፡ እነዚህን ድል የሚነሣ፤ በጎቹን ምእመናን ከተኩላ፣ ከአንበሳና፣ ከድብ አፍ የሚታደግ
ታማኝ አገልጋይ ማነው? ከምእመናን ተግዳሮት የሚያርቅ ፈጣሪዬ ከመከራ ያድነኛል ብሎ የሚታመን የኢ አማንያን ብዛት
የማያስፈራው ማን ነው? ከትንሽነቱ እስከ ታላቅነቱ የታመነ አገልጋይ ማነው? ለተሾመበት ሓላፊነት ታማኝ ማነው?
አሁንም ዓለማችን ከሥጋውያን ባለ ሥልጣናትም ኾነ ከመንፈሳውያን መሪዎች የምትሻው ታማኝ ሰው ነው፡፡ በሙስና
ያልተዘፈቀ፤ ጉቦ አይኑን ያላጨለመበት፤ ለመንጋው አርአያና ምሳሌ የሚኾን ሰው፤ ታማኝ አገልጋይ ማለት እርሱ ነው፡፡
በመሐላ የተቀበለውን የአገልግሎት ሓላፊነት የማይዘነጋ ጳጳስ፣ ቄስ፣ ዲያቆን፣ ሰባኪ፣ መምህር፣ ሐኪም፣ ዳኛ፣
ነጋዴ፣ ተማሪ፣ ወታደር፣ የቤት ሠራተኛ፣ የቢሮ ሠራተኛ ታማኝ መኾን አለበት፡፡
መንጋው በክህደት ሲጠፋ ዝም ብሎ የሚያይ ጳጳስ፣ ቄስ፣ ዲያቆን፣
መምህር፣ ሰባኪ፣ ታማኝ አይደለም፡፡ ታማሚው እየተሰቃየ የሚዝናና ሐኪም ታማኝ አይደለም፡፡ ፍርድ የሚያጎድል፤
ድሆችን የሚበድል፤ ለደሃ አደጎች የማይፈርድ ዳኛ ታማኝ አገልጋይ አይደለም፡፡ ቅቤ በሙዝ እና በድንች ቀላቅሎ፣
በርበሬ በሸክላ አፈር ጨምሮ፣ ሌሎችን አጭበርብሮ የሚሸጥ ነጋዴ ታማኝ አገልጋይ አይደለም፡፡ እየነገደ ያለው በሰው
ሕይወት መኾኑን መዘንጋት የለበትም፡፡ ዅሉም እንደየአቅሙ በተሰጠው የአገልግሎት ዘርፍ ታማኝ መኾን አለበት፡፡
ዮሴፍ
ዮሴፍ ለወንድሞቹ ምግባቸውን ተሸክሞ የእርሱ ስንቅ ቢያልቅ
የወንድሞቹን ስንቅ ያልበላ በትንሹ የታመነ ሰው ነበር፡፡ ወንድሞቹ ሸጠውት በቤተ ጲጥፋራ በሚያገለግልበት ጊዜም
ታማኝ ነበር፡፡ ታማኝነቱ በጲጥፋራ ቤት ጌታ አድርጎታል፡፡ ‹‹ዮሴፍ ተሸጠ፤ አገልጋይም ኾነ፡፡ እግሮቹ በእግር ብረት ሰለሰሉ፡፡ ሰውነቱም ከብረት አመለጠች፡፡ ቃሉ ሳይደርስ የእግዚአብሔር ቃል ፈተነው፡፡ ንጉሥ ላከ፤ ፈታውም የሕዝብ አለቃ አድርጎ ሾመው፡፡ የቤቱም ጌታ አደረገው፡፡ በገንዘቡ ዅሉ ላይ ገዢ አደረገው፡፡ አለቆቹን እንደ እርሱ ይገሥፅ ዘንድ፤ ሽማግሌዎችን እንደ እርሱ ጥበበኞች ያደርጋቸው ዘንድ፤›› ተብሎ እንደ ተነገረለት (መዝ.፻፬፥፲፯)፡፡
በዚህ ኹኔታ የነበረው ዮሴፍ የጌታው ሚስት ሲወጣ ባቱን፣ ሲገባ ደረቱን እያየች ዐይኗን ጣለችበት፤ በዝሙት አይን ተመለከተችው፡፡ ‹‹ከእኔ ጋር ተኛ›› እያለችም በየቀኑ አስቸገረችው፡፡ እርሱ ግን ‹‹እምቢ›› አላት፡፡ ለጌታው ሚስትም፡- ‹‹እነሆ ጌታዬ በቤቱ ያለውን ዅሉ ለእኔ በእጄ አስረክቦኛል፡፡ በቤቱ ያለውን ምንም የሚያውቀው የለም፡፡ በዚህ ቤት ከእኔ የሚበልጥ ሰው የለም፡፡ ሚስቱ ስለ ኾንሽ ከአንቺ በቀር ያልሰጠኝ ነገር የለም፡፡ እንዴት ይህን ትልቅ ክፉ ነገር አደርጋለሁ? እንዴትስ በእግዚአብሔር ፊት ኀጢአትን እሠራለሁ?›› በማለት የዝሙት ጥያቄዋን ውድቅ አደረገባት (ዘፍ.፴፱፥፯)፡፡
በዮሴፍ ታማኝነት የጌታው ቤት ተባርኳል፡፡ ሀብቱ በዝቷል፡፡
በታማኝነቱ በቤቱ ያለውን ዅሉ ተረክቦ ነበር፡፡ የቀረበለት ፈተና ግን ከባድ ነበር፤ ኾኖም ግን በታማኝነቱ ለማለፍ
ችሏል፡፡ ዮሴፍ በታማኝ አገልጋይነቱ በመጣበት መከራ ቢታሰርም እንኳን ያለ ሹመት አላደረም፤ የእስረኞች አለቃ
ነበር፡፡ ከእስር ቤት ሲወጣም ግብጽን በሙሉ መርቷል፡፡ በግብጻውያን ላይ ተሾሟል፤ በጥቂቱ ታምኗልና፡፡ ‹‹በጥቂቱ የታመነ በብዙ ይሾማል››
እንዲል (ማቴ.፳፭፥፳፬)፡፡ዛሬ በእየአንዳንዱ ጓዳ እንደ እሳት የሚያቃጥሉ አገልጋዮች ናቸው ያሉት፡፡ ልጅ በፈላ
ውኃ የሚቀቅሉ ናቸው የሚበዙት፡፡ እንኳን በዅሉ ገንዘብ ለመሾም በጥቃቅን ዕቃዎች እንኳን የሚታመን ሰው ጠፍቷል፡፡
ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ፡- ‹‹አቤቱ አድነኝ፤ ደግ ሰው አልቋልና፡፡ ከሰው ልጆችም መተማመን ጎድሏልና፤›› በማለት እንደ ተናገረው በመካከላችን መተማመን የለም (መዝ.፲፩፥፩)፡፡
እናም ከእነዚህ ሦስት ታማኝ አገልጋዮች (ሙሴ፣ ዳዊት እና
ዮሴፍ) ሕይወት ዅሉም የሰው ልጅ ታማኝ አገልጋይነት የሚያሰጠውን ክብርና ጸጋ ተመልክቶ በታማኝነት ማገልገል
ይገባዋል፡፡ ታማኝ መኾን መጀመሪያ የሚጠቅመው ራስን ነው፤ ከዚያ በኋላ ለአገር፣ ለወገን፣ ለቤተ ክርስቲያን፣
ላመኑትም ላላመኑትም ዅሉ ጠቃሚ ይኾናል፡፡ በመጨረሻም የጽድቅ አክሊልን ይቀዳጃል፤ መንግሥተ ሰማያትን ያወርሳል፡፡
ታማኝነት በሰውም፣ በእግዚአብሔርም ፊት ያስከብራልና፡፡ ጻድቃን፣ ሰማዕታት ቅዱሳን በታማኝነት በማገልገላቸው
ፈጣሪአቸውን ደስ አሰኝተው ከብረዋል፡፡
በሓላፊው ገንዘብ ያልታመኑት እነይሁዳ፣ ሐናንያ እና ሰጲራ
የደረሰባቸውን ጉዳት አይተናል፡፡ አካን ወልደ ከርሚንም ተመሳሳይ ቅጣት ደርሶበታል (ሐዋ.፭፥፩-፳፭)፡፡ ስለ ኾነም
ዅሉም በተሰማራበት የአገልግሎት መስክ ታማኝ አገልጋይ ኾኖ ‹‹አንተ በጎ ታማኝ አገልጋይ በጥቂቱ ታምነሃል፤ በብዙ
እሾምሀለሁ፤›› የሚለውን የጌታውን የምስጋና ቃል ለመስማት ተዘጋጅቶ መጠበቅ ይገባዋል፡፡ መልካም አገልግሎት
አገልግለን፣ በእግዚአብሔር ‹አግብርት ኄራን፤ ታማኝ አገልጋዮች› እንድንባል፤ መንግሥቱንም እንድንወርስ አምላካችን ይርዳን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡
ወረደ መንፈስ ቅዱስ
ሰኔ ፲፯ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም
በዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው
መንፈስ ቅዱስ ማለት ከሦስቱ አካላት (ከቅድስት ሥላሴ) አንዱ፤ የእግዚአብሔር አብ፣ የእግዚአብሔር ወልድና የራሱም አካላዊ እስትንፋስ የኾነው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡
*ወረደ መንፈስ ቅዱስ* የሚለው የግእዝ ዓረፍተ ነገርም *መንፈስ
ቅዱስ ወረደ* የሚል ትርጕም ያለው ሲኾን፣ ይህ ሲባልም በሰዉኛ ቋንቋ ከከፍታ ወደ ዝቅታ፣ ከሩቅ ወደ ቅርብ
መምጣቱን ወይም መውረዱን ሳይኾን የእግዚአብሔር መንፈስ በሐዋርያት ላይ አድሮ ሰማያዊ ሀብትን፣ ዕውቀትን፣ ጥበብን
መግለጹንና ልዩ ልዩ ጸጋን ማደሉን ያመላክታል፡፡
ይህ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ለጊዜው ለሐዋርያት ቢሰጥም፣ በእነርሱ ላይ ብቻ ሳይገደብ እስከ ዕለተ ምጽአት ድረስ በምእመናን ላይም አድሮ ይኖራል፡፡
ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ ወረደ የሚለው ትምህርት መንፈስ ቅዱስን
በቦታ፣ በጊዜና በወሰን መገደቡን አያመለክትም፡፡ የእግዚአብሔር መንፈስ በዓለሙ ኹሉ የሞላ ነውና፡፡ በሰው ላይ
አድሮ ጥበብን ሲገልጽ ግን ሞላ፤ አደረ፤ ወረደ ተብሎ ይነገራል፡፡ ይኸውም ሥራዉን በሰው ላይ መግለጡን፣ ጸጋዉንም
ማብዛቱን ለማመልከት የሚያገለግል ቋንቋ ነው፡፡
ከላይ እንደ ተገለጸው እግዚአብሔር በቅዱሳን ሐዋርያት ላይ
ፍርኃትን አስወግዶ ጥብዓትን (ጭካኔን)፣ ስጋትን አጥፍቶ ቈራጥነትን (ድፍረትን) ማሳደሩን፤ እንደዚሁም ሰማያዊ
ሀብትን፣ ዕውቀትን፣ ጥበብንና ጸጋን እንዲያገኙ ማድረጉን፤ በዚህም ሐዋርያት ለስብከተ ወንጌልና ለሰማዕትነት
የሚያበቃ ቅድስና ላይ መድረሳቸዉን ያመለክታል፡፡
መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት ላይ የወረደው ጌታችን መድኀኒታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ በተወለደባት፣ በተጠመቀባትና ከሞታን ተለይቶ በተነሣባት በዕለተ ሰንበት (በሰንበት ክርስቲያን)
ሲኾን፣ መንፈስ ቅዱስ ከወረደበት ሰንበት (ከኀምሳኛው ቀን) ጀምሮ እስከሚቀጥለው ሰንበት ያለው ጊዜም (ስምንቱ
ቀናት) ዘመነ ጰራቅሊጦስ ወይም ሰሙነ ጰራቅሊጦስ ይባላል፡፡ ይህም መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት ላይ ስለ መውረዱና
በምእመናን ላይ ስለ ማደሩ የሚነገርበት ወቅት ነው፡፡
በዚህ ሰሙን በቤተ ክርስቲያን የሚነገረው ቃለ እግዚአብሔር፣
የሚሰጠውም ትምህርት የመንፈስ ቅዱስን በሐዋርያት ላይ መውረድ የሚመለከት ነው፡፡ ስለዚህም ከኀምሳኛው ቀን (ከበዓለ
ጰራቅሊጦስ) ቀጥሎ በሚመጣው እሑድ (በስምንተኛው ቀን) በሌሊት በሊቃውንቱ የሚዘመረው መዝሙር፡- *ወረደ መንፈስ
ቅዱስ ላዕለ ሐዋርያት ከመ ዘእሳት ወተናገሩ በነገረ ኵሉ በሐውርት* የሚል ሲኾን፣ ትርጕሙም መንፈስ ቅዱስ በእሳት
አምሳል በሐዋርያት ላይ መውረዱንና በእርሱ ኃይል በዓለሙ ኹሉ ቋንቋዎች መናገራቸዉን የሚያስረዳ ነው፡፡
በዚህ ዕለት በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎችም፡- የሚከተሉት ናቸው፤ ኤፌ.፬፥፩-፲፯፤ ፩ኛዮሐ.፪፥፩-፲፰፤ ሐዋ.፪፥፩-፲፰፤ መዝ.፷፯፥፲፰ (ምስባክ)፤ ዮሐ.፲፬፥፩-፳፪ (ወንጌል)፡፡
የምንባባቱ ፍሬ ዐሳብም የጳውሎስ መልእክት፡- እያንዳንዳችን
መንፈስ ቅዱስ በገለጸልን መጠን የየራሳችን ልዩ ልዩ ጸጋ እንዳለን፤ የዮሐንስ መልእክት፡- የእግዚአብሔርን ፈቃድ
የሚፈጽም ለዘለዓለም ሕያው እንደ ኾነ፤ የሐዋርያት ሥራ፡- መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት ላይ እንደ ወረደና በዓለሙ ኹሉ
ቋንቋዎች መናገር እንደቻሉ፤ መዝሙረ ዳዊት (ምስባኩ)፡- እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ልዩ ልዩ ጸጋን እንደሚሰጥ፤
የዮሐንስ ወንጌል፡- እግዚአብሔር እኛን ልጆቹን እንደ ወላጅ አልባ እንደማይተወን ያስረዳሉ፡፡
ቅዳሴውም ቅዳሴ ዲዮስቆሮስ ሲኾን፣ ይህም ምሥጢረ ሥላሴን፣ የጌታችንን ሰው መኾን፣ ሕማሙን፣ ሞቱን፣ ትንሣኤዉን፣ ዕርገቱንና መንፈስ ቅዱስን መላኩን ይናገራል፡፡
ቅድስት በኾነች በጽርሐ ጽዮን በሐዋርያት ላይ የወረደው የእግዚአብሔር አብ ጸጋ፣ የእግዚአብሔር ወልድ ፍቅር፣ የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አንድነት በኹላችን ላይ ይደር፤ እጽፍ ድርብም ይኹን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡
ጰራቅሊጦስ ከሣቴ ምሥጢር
ሰኔ ፲፯ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም
በመምህር ማዕበል ፈጠነ
ጰራቅሊጦስ ማለት ከሣቴ ምሥጢር ማለት ነው፡፡ ይኸውም በግብሩ ታውቋል፡፡ በበዓለ ጰራቅሊጦስ አበው ሐዋርያት ብዙ ምሥጢር በመንፈስ ቅዱስ ተገልጾላቸው ብሉይና ሐዲስን ተርጕመዋል፡፡
ማለትም ወደ ኋላ ተመልሰው *እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤
በመጨረሻው ቀን ሥጋ በለበሰ ኹሉ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ፡፡ ልጆቻችሁ ትንቢት ይናገራሉ፤* ተብሎ የተነገረውን
ትንቢት ጠቅሰው፣ በመብረቅ መጽሔት ተሞልተው ወደ ፊት የሰው ልጅ በሃይማኖትና በምግባር የሚወርሳትን የመንግሥተ
ሰማይን ተስፋ አብሥረዋል /ሐዋ.፪፥፲፯፤ ኢዩ.፪፥፲፰/፡፡
ከቀደመው ቋንቋቸው ሌላ ፸፩ ቋንቋ ተገልጾላቸው በ፸፪ ቋንቋ
አስተምረዋል፡፡ ይህ ሲባል ግን በዘመኑ የነበረው ሕዝብ እርስበርስ ይግባባቸው የነበሩት ቋንቋዎች ፸፪ ስለ ነበሩ
ነው እንጂ መንፈስ ቅዱስ ከዚህም በላይ ቋንቋዎችንና ጥበብን መግለጽ እንደሚቻለው ልብ ማለት ያስፈልጋል፡፡ ጥንተ
ነገሩስ እንደምን ነው ቢሉ ጌታችን በዚህ ዓለም ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ወንጌለ መንግሥትን አስተምሮ በመልዕልተ
መስቀል ተሰቅሎ፣ በሲኦል የነበሩ ነፍሳተ ሙታንን ከዲያብሎስ ባርነት ነጻ አውጥቶ የሲኦልን በር ዘግቷል፡፡
በዚህ ዓለም ደግሞ ብርሃነ መለኮቱን ገልጾ ከሙታን ተለይቶ
ከተነሣ በኋላ ፵ ቀን ለአበው ሐዋርያት በመጽሐፈ ኪዳን የተገለጹ ረቂቅ ምሥጢራትን አስተምሮ መንፈስ ቅዱስ ትርጕሙን
እንደሚነግራቸው፤ በሰዓቱ ግን መሸከም እንደማይችሉ ነግሯቸው ባረገ በ፲ኛው ቀን ለ፲፪ቱ ሐዋርያት፣ ለ፸፪ቱ
አርድእትና ለ፴፮ቱ ቅዱሳት አንስት በአጠቃላይ ለ፻፳ው ቤተሰብ መንፈስ ቅዱስን ልኮላቸዋል፡፡ በዚህ ጊዜ በአዲስ
ልሳን መናገር ጀምረዋል፡፡
አዲስ ልሳን ሲባልም በዓለም የሌለ ሌላ ባዕድ ቋንቋ ማለት
አይደለም፡፡ የዓለም ቋንቋዎች ኹሉ በመንፈስ ቅዱስ እሳትነት በሐዋርያት አንደበት ተዋሐዱ፤ በልቦናቸው አደሩ፤
ሐዋርያት በዕውቀት ታነፁ ማለት ነው እንጂ፡፡ እንደሚታውቀው የሰው ልጅ የዓለማትን ቋንቋ በሙሉ ተምሮ ለማወቅ
አይቻለዉም፡፡ አበው ሐዋርያት ግን ከሥጋዊ፣ ከደማዊ መምህር በመማር፤ መልክአ ፊደል በማጥናት ሳይኾን፣ መንፈስ
ቅዱስ ገልጾላቸው አንደበታቸው ሰይፍ፣ ልሳናቸው ርቱዕ፣ ኾኖ በልዩ ልዩ ቋንቋዎች መናገር ችለዋል፡፡
ነገር ግን ሐዋርያት ባዕድ ቋንቋ አላመጡም፡፡ ጌታም የገለጸላቸው
የዚህ ዓለም ብርሃን እንደመኾናቸው በዓለም የሚነገሩ ቋንቋዎችን ነው፡፡ ሰው የማይሰማውን ቋንቋ ቢናገሩ ኖሮ
ከነፋስ ጋር እንደመናገር ይቈጠር ነበር /፩ኛቆሮ.፲፬፥፱/፡፡ ይህንንም ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ *ወአኀዙ ይንብቡ
ዘዘዚአሆሙ በነገረ ኵሉ በሐውርት በከመ ወሀቦሙ መንፈስ ቅዱስ፤ ኹሉም መንፈስ ቅዱስን ተሞሉ፡፡ ይናገሩ ዘንድ
መንፈስ ቅዱስ እንዳደላቸው መጠንም እየራሳቸው በአገሩ ኹሉ ቋንቋ ይናገሩ ጀመሩ፤* በማለት ገልጾታል
/ሐዋ.፪፥፬/፡፡
በዚህ ጊዜ ቤተ አይሁድ በከፊል አንጎራጎሩ፤ አሕዛብ ተደመሙ፡፡
ሐዋርያትን በገዛ ቋንቋቸው ሲናገሩ ሰምተው *እኛ የጳርቴ፣ የሜድ፣ የኢላሜጤም ሰዎች ስንኾን፣ በእኛ ቋንቋ እነሆ
የእግዚአብሔርን ጌትነት ሲናገሩ እንሰማዋቸዋልን* ሲሉ አደነቁ፤ ከእግራቸው ሥርም ወደቁ፡፡ በቅፅበትም ሦስት ሺህ
ነፍሳት አምነው ተጠመቁ፡፡
በዚህ ዘመን በግላቸው ቤተ እምነት መሥርተው የሚኖሩ ባዕዳን
*መንፈስ ቅዱስ ወረደልን፤ አዲስ ልሳን ተገለጠልን፤ እልል በሉ፤* እያሉ ዐይናቸውን ይጨፍናሉ፤ አእምሯቸውን
ይስታሉ፡፡ በአንደበታቸውም እነርሱ የማያውቁትን፤ ሌላ ሰውም ሊሰማው የማይችለዉን ትርጕም የሌለዉን ጩኸት፣ እነርሱ
ልሳን የሚሉትን ድምፅ ያነበንባሉ፡፡
የመንፈስ ቅዱስ ዓላማ ሰዎች እርስበርስ እንዲግባቡ ትርጕም
ያለዉን ቋንቋ መግለጽ እና ኹሉም በየቋንቋው የእግዚአብሔርን የምሥራች ቃል እንዲማር፣ እንዲያውቅና እንዲረዳ ማድረግ
ነው፡፡ ልሳን ማለትም ሰው ሊረዳውና ሊግባባት የሚችል ቋንቋ ማለት እንጂ ድምፅ በማውጣት ብቻ የሚገለጽ ጩኸት
አይደለም፡፡ መናፍቃኑ ልሳን የሚሉት ግን ይህንኑ ዓይነት ባዶ ጩኸት ነው፡፡ ይህም ከሰይጣን እንጂ ከመንፈስ ቅዱስ
እንዳልኾነ ያጠይቃል፡፡
የመንፈስ ቅዱስ የሆነው አዲስ ልሳን ግን ትናንት በአበው
ሐዋርያት ዘመን የነበረ፤ ዛሬም በእኛ ዘመን ያለ፤ ለመጭው ትውልድም የሚተላለፍ ሕያው ልሳን ነው፡፡ ለምን ቢሉ
ከሣቴ ምሥጢሩ (ምሥጢር ገላጩ) መንፈስ ቅዱስ ነውና፡፡
እንግዲህ በነቢያት የተነገረው፣ በሐዋርያት ልቡና በእሳት አምሳል
የተገለጠው ምሥጢረ መንፈስ ቅዱስ ይህ ነው፡፡ ይህ ምሥጢር ከትውልድ ወደ ትውልድ ተላልፎ በሐዋርያት ልቡና
ቀርቷል፤ ከሐዋርያት ልቡና ያልደረሰው ደግሞ በልበ መንፈስ ቅዱስ ቀርቷል፡፡ ዓውደ ትምህርቱ ይህ ነው፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡
‹‹አንተ በጎና ታማኝ አገልጋይ›› ማቴ:25
መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ
ላለው ሁሉ ይሰጠዋልና ይበዛለትማል:: ከሌላው ግን ያው ያለው እንኳ ይወሰድበታል፡፡ የማይጠቅመውንም ባሪያ
በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት:: በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል፡፡›› የሚል ነው፡፡ መክሊት ጥንት የክብደት
መለኪያ ነበር:: አንድ መክሊት 30 ኪሎ ግራም ያህል ነው፡፡ በዚህ ምሳሌ ላይ እንደተገለጸውም መክሊት የሚለው ቃል
ገንዘብን ያመለክታል፡፡
ይህ የመክሊቱ ባለቤት የተባለው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን የተሰጣቸውን ኃላፊነት ለተወጡት ሁሉ እርሱ ፍጹም ዋጋን የሚሰጣቸው መሆኑን ያመለክታል፡፡ ይህም ሁኔታ ‹‹ መልካም አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃል በብዙ እሾምሃለሁ፡፡ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ›› በሚል ተገልጧል፡፡ ይህ ቃል በሃይማኖት ለእግዚአብሔር የታመኑ ሁሉ ወደ ፍጹም ደስታ ወደ መንግሥተ ሰማያት ለመግባት ለሚያደርጉት ጉዞ እጅግ ተስፋ የሆነ ቃል ነው፡፡
በዚህ ላይ እንደተገለጸው እግዚአብሔር አምላክ ለሁላችንም እርሱን የምናገለግልበትንና ለእርሱ በመታመን ዘላለማዊ ክብርን የምናገኝበትን ዕውቀትን ማስተዋልን’ ሀብትን’ ዓቅም ወይም ጉልበትን ሌሎችንም ልዩ ልዩ ስጦታዎችን ለእኛ ለሰው ልጆች እንደየዓቅማችን መጠን ሰጥቶናል፡፡
እነዚህ ሁሉ ነገሮች የሥጋችንን ምኞት እንድንወጣባቸው የተሰጡ ሳይሆኑ ነፍሳችን የምትከብርበትን መልካም ሥራን የምንሠራባቸው ናቸው፡፡
በመሆኑም እርሱ በሰጠን የአገልግሎት ጸጋ በታማኝነት በማገልገል በተሰጠን ነገር ሁሉ መንፈሳዊውን ሀብት የምናተርፍ ልንሆን ይገባናል፡፡ ምክንያቱም እኛ የተጠራ ነው ፍሬ ልናፈራና ሌላውንም ልናተርፍ መልካም ሥራን ልንሠራ እንጅ የሥጋችንን ፈቃድ በመከተል የኃጢኣት ባሮች ልንሆን አይደለም፡፡
ህዳር 15 ቀን 2007 ዓ᎐ም
ልዑል እግዚአብሔር አምላካችን በክቡር ዳዊት አድሮ፤ “እከሥት
በምሳሌ አፉየ፤ ወእነግር አምሳለ ዘእምትካት፤ አፌን በምሳሌ እከፍታለሁ፤ ከቀድሞ ጀምሮ ያለውንም ተምሳሌት
እናገራለሁ” ብሏል፡፡ /መዝ. 77፡2/
በዚሁ መሠረት ጌታችን ወንጌለ መንግሥተ ሰማያትን በልዩ ልዩ ምሳሌ አስተምሯል፤ በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 25 ሁለት ምሳሌያትና አንድ ትንቢት ቀርበዋል፡፡
በዚሁ መሠረት ጌታችን ወንጌለ መንግሥተ ሰማያትን በልዩ ልዩ ምሳሌ አስተምሯል፤ በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 25 ሁለት ምሳሌያትና አንድ ትንቢት ቀርበዋል፡፡
ከምሳሌያቱ የመጀመሪያው በዐሥሩ ደናግል አንጻር የቀረበው ሲሆን
ሌላኛው ደግሞ ወጥተው ወርደው ነግደው ያተርፉበት ዘንድ ገንዘቡን ስለሰጠ ነጋዴ የሚናገረው ነው፡፡ ትንቢቱም ስለ
ኅልቀተ ዓለም የተነገረ ነው፡፡ እንግዲህ በዚህ ዕትማችን ነግደው እንዲያተርፉበት ከጌታቸው የተሰጣቸውን መክሊት
ስለተቀበሉት አገልጋዮች እንመለከታለን፡፡ ፈጣሪያችን ለብዎውን ማስተዋሉን ያድለን፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ ለደቀ መዛሙርቱ ያስተማራቸውን ምሳሌያዊ ትምህርቶችን በሰፊው ተጽፎ እናገኛለን፡፡
የእነዚህ ትምህርታዊ ምሳሌዎች መሠረታዊ ሀሳብና ዓላማ የእግዚአብሔርን መንግሥት የምናገኝበትን የታማኝነትን ሥራን እንዴት መሥራት እንደሚገባንና እንደምንችል ማስተማር ነው፡፡
ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ መንግሥተ ሰማያት ምሥጢር ያስተማራቸው ብዙ ምሳሌዎች ያሉ ሲሆን ከእነዚህ ብዙ ምሳሌዊ ትምህርቶች መካከል በማቴዎስ ወንጌልም 25 ላይ እንዲያተርፉበት መክሊት ስለተሰጣቸውና ወጥተው ወርደው ሌላ አትረፈው በጌታቸው ስለተመሰገኑት ቸርና መልካም አገልጋዮች፣ እንዲሁም መክሊቱን በመቅበሩ ምክንያት በጌታው ስለተወቀሰውና ፍርድን ስለተቀበለው ሰው ታሪክ፣ የታሪኩም ምሥጢር ምን እንደሚመስል ነው፡፡
ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ መንግሥተ ሰማያት ምሥጢር ያስተማራቸው ብዙ ምሳሌዎች ያሉ ሲሆን ከእነዚህ ብዙ ምሳሌዊ ትምህርቶች መካከል በማቴዎስ ወንጌልም 25 ላይ እንዲያተርፉበት መክሊት ስለተሰጣቸውና ወጥተው ወርደው ሌላ አትረፈው በጌታቸው ስለተመሰገኑት ቸርና መልካም አገልጋዮች፣ እንዲሁም መክሊቱን በመቅበሩ ምክንያት በጌታው ስለተወቀሰውና ፍርድን ስለተቀበለው ሰው ታሪክ፣ የታሪኩም ምሥጢር ምን እንደሚመስል ነው፡፡
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህንን ምሳሌ የተናገረው በሚከተለው
መልኩ ነበር ‹‹ወደ ሌላ ሀገር የሚሄድ ሰው ባሮቹን ጠርቶ ያለውን ገንዘብ እንደሰጣቸው እንዲሁ ይሆናልና ለእንዳንዱ
እንደ ዓቅሙ ለአንዱ አምስት መክሊት ለአንዱ ሁለት ለአንዱም አንድ ሰጠና ወደ ሌላ ሀገር ወዲውኑ ሄደ፡፡ አምስት
መክሊትም የተቀበለው ሄደ ነገደበት ሌላም አምስት አተረፈ እንዲሁም ሁለት የተቀበለው ሌላ ሁለት አተረፈ፡፡ አንድ
የተቀበለው ግን ሄዶ ምድርን ቆፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ፡፡
ከብዙ ዘመንም በኋላ የእነዚያ ባሮች ጌታ መጣና ተቆጣጠራቸው፡፡
ከብዙ ዘመንም በኋላ የእነዚያ ባሮች ጌታ መጣና ተቆጣጠራቸው፡፡
አምስት መክሊት የተቀበለውም ቀረበና ሌላ አምስት መክሊት
አስረክቦ፡- ጌታ ሆይ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፡ እነሆ ሌላ አምስት መክሊት አተረፍሁበት አለ፡፡ ጌታውም፡-
መልካም አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃል በብዙ እሾምሃለሁ:: ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው፡፡ ሁለት
መክሊት የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፡- ጌታ ሆይ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፡፡ እነሆ ሌላ ሁለት መክሊት አተረፍሁበት
አለ፡፡ ገታውም፡- መልካም አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃልና በብዙ እሾምሃለሁ:: ወደ ጌታህ ደስታ ግባ
አለው፡፡
አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፡- ጌታ ሆይ ካልዘራህበት የምታጭድ ካልበተንህባትም የምትሰበስብ ጨካኝ
ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ ፈራሁም ሄጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት እነሆ መክሊትህ አለህ አለው፡፡ ጌታውም መልሶ
እንዲህ አለው፡- አንተ ክፉና ሃኬተኛ ባሪያ ካልዘራሁበት እንዳጭድ ካልበተንሁባትም እንድሰበስብ ታውቃለህን::
ስለዚህ ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ልትሰጠው በተገባህ ነበር:: እኔም መጥቼ ያለኝን ከትርፉ ጋር እወስደው ነበር፡፡
ስለዚህ መክሊቱን ውሰዱበት አሥር መክሊትም ላለው ስጡት::
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ምሳሌ ውስጥ እርሱን የምናገለግል
ሁላችን አንደየዓቅማችን ማድረግ የሚገባንን መንፈሳዊ የአገልግሎት ሥራንና በአገልግሎታችን ውጤታማ በመሆናችንም
ከእርሱ የምናገኘውን ዘላለማዊ ክብርና ዋጋን እንዲሁም መሥራት የሚገባንን ባለማድረጋችንም ምክንያት የሚገጥመንን
መለኮታዊ ቅጣትን አመልክቶናል፡፡ በዚህ ምሳሌ ውስጥ ባለ አምስት የተባለው ፍጹም ትምህርት ተምሮ ሌላውን መክሮ
አስተምሮ ራሱን አስመስሎ ያወጣነው፡፡
በተመሳሳይም ባለሁለት የተባለው ፍጹም ትምህርት ተምሮ ሌላውን
መክሮ አስተምሮ ራሱን አስመስሎ ያወጣ ሲሆን ባለአንድ የተባለው ደግሞ ተምሮ ሳያስተምር የቀረ ሰው ነው፡፡ በመሆኑም
ባለአምስትና ባለሁለት መክሊት የሆኑት ወጥተው ወርደው ደክመው’ መከራ መስቀልን ሳይሰቀቁና ሳይፈሩ’ ነፍሳቸውን
ለታመነው አምላክ አደራ በመስጠት የተማሩትን ፍጹም ትምህርት ለሌላው አስተምረው ሌላውን አንደራሳቸው የተማረ
አድርገው ሲያወጡ ባለአንድ የተባለው ግን አላውያን እሳት ስለት አሳይተው ቢያስክዱኝ መናፍቃን ተከራክረው ምላሽ
ቢያሳጡኝ ብሎ ፈርቶ ሃይማኖቱን በልቡ ከመያዝ በቀር የተማረውን ትምህርት ለሌላው ሊያስተምርና የተሰጠውን አደራንም
ሊወጣ አልወደደም፡፡
በምሳሌው ውስጥ እንደተገለጠው ሌላ አምስትና ሁለት ያተረፉት በተሰጣቸው መክሊት ሌላ ማትረፋቸውን ለጌታቸው በገለጡ ጊዜ የመክሊቱ ባለቤት እጅግ አድርጎ እንዳመሰገናቸው ከላይ አንብበናል፡፡ይህ የመክሊቱ ባለቤት የተባለው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን የተሰጣቸውን ኃላፊነት ለተወጡት ሁሉ እርሱ ፍጹም ዋጋን የሚሰጣቸው መሆኑን ያመለክታል፡፡ ይህም ሁኔታ ‹‹ መልካም አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃል በብዙ እሾምሃለሁ፡፡ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ›› በሚል ተገልጧል፡፡ ይህ ቃል በሃይማኖት ለእግዚአብሔር የታመኑ ሁሉ ወደ ፍጹም ደስታ ወደ መንግሥተ ሰማያት ለመግባት ለሚያደርጉት ጉዞ እጅግ ተስፋ የሆነ ቃል ነው፡፡
በዚህ ላይ እንደተገለጸው እግዚአብሔር አምላክ ለሁላችንም እርሱን የምናገለግልበትንና ለእርሱ በመታመን ዘላለማዊ ክብርን የምናገኝበትን ዕውቀትን ማስተዋልን’ ሀብትን’ ዓቅም ወይም ጉልበትን ሌሎችንም ልዩ ልዩ ስጦታዎችን ለእኛ ለሰው ልጆች እንደየዓቅማችን መጠን ሰጥቶናል፡፡
እነዚህ ሁሉ ነገሮች የሥጋችንን ምኞት እንድንወጣባቸው የተሰጡ ሳይሆኑ ነፍሳችን የምትከብርበትን መልካም ሥራን የምንሠራባቸው ናቸው፡፡
በመሆኑም እርሱ በሰጠን የአገልግሎት ጸጋ በታማኝነት በማገልገል በተሰጠን ነገር ሁሉ መንፈሳዊውን ሀብት የምናተርፍ ልንሆን ይገባናል፡፡ ምክንያቱም እኛ የተጠራ ነው ፍሬ ልናፈራና ሌላውንም ልናተርፍ መልካም ሥራን ልንሠራ እንጅ የሥጋችንን ፈቃድ በመከተል የኃጢኣት ባሮች ልንሆን አይደለም፡፡
ከላይ እንደተመለከትነው በልዑል አምላክ በእግዚአብሔር አንደበት
አንተ በጎ ታማኝ አገልጋይ በጥቂቱ ታምነሃልና በብዙ እሾምሃለሁ መባልን የመሰለ አስደሳችና አስደናቂ ነገር የለም፡፡
ይህ ደግሞ የሚገኘው ሃይማኖትን በሥራ በመግለጥ እንጅ ሃይማኖትን በልቦና በመያዝ ብቻ አይደለም፡፡ ከእነዚህም
እንደ አቅማቸው መክሊት ተሰጥቷቸው ሌላ መክሊት ካተረፉት በጎና ታማኝ አገልጋዮች ከተባሉት የምንማረው እውነታ ይህ
ነው፡፡ ስለዚህም በብዙ ለመሾም በጥቂቱ መታመን ግድ ነው፡፡
አንድ መክሊት የተሰጠውን ሰው ስንመለከተው ጌታውን ጨካኝ አድርጎ ከመቁጠር ውጪ በተሰጠው መክሊት ወጥቶ ወርዶ ሊያተርፍ አልወደደም፡፡ መክሊቱንም ባስረከበ ጊዜ በጌታው ላይ የተናገራቸው ቃላት የእርሱን አለመታዘዝና አመጸኝነት ይገልጡ ነበር፡፡
አንድ መክሊት የተሰጠውን ሰው ስንመለከተው ጌታውን ጨካኝ አድርጎ ከመቁጠር ውጪ በተሰጠው መክሊት ወጥቶ ወርዶ ሊያተርፍ አልወደደም፡፡ መክሊቱንም ባስረከበ ጊዜ በጌታው ላይ የተናገራቸው ቃላት የእርሱን አለመታዘዝና አመጸኝነት ይገልጡ ነበር፡፡
በመሆኑም ይህ ሰው በጥቂቱ መታመን ያቀተውና በአስተሳሰቡ
ደካማነት እጅግ የተጎሳቆለ ሰው ነው፡፡ በዚህ ምሳሌ መሠረት ይህ ባለአንድ የተባለው ሰው ዓላውያን እሳት ስለት
አሳይተው ቢያስክዱኝ መናፍቃን ተከራክረው መልስ ቢያሳጡኝ በማለት ሃይማኖቱን በልቡ ሸሽጎና ቀብሮ ከመያዙ ባሻገር
በጌታ ፊት በድፍረት ቆሞ አንተ ሕግ ሳትሠራ በአዕምሮ ጠባይዕ አውቃችሁ’ መምህርም ሳትሰጥ በሥነ ፍጥረት
ተመራምራችሁ በሠራችሁ ብለህ የምትፈርድ ጽኑ ጨካኝ መሆንክን አውቃለሁና ዓላውያን እሳት ስለት አሳይተው ቢያስክዱኝ
መናፍቃን ተከራክረው መልስ ቢያሳጡኝ ብየ ፈርቼ ሃይማኖቴን በልቡናየ ይዠዋለው በአዕምሮየ ጠብቄዋለሁ የሚል
ሃይማኖቱን ግን በሥራ የማይገልጥ ሰነፍ ሰውን ያመለክታል፡፡
ለዚህ ዓይነት ሰው የጌታ መልስ ደግሞ በምሳሌው መሠረት
የሚከተለው ነው፡፡ እኔ ሕግ ሳልሠራ በአዕምሮ ጠባይዕ አውቃችሁ መምህር ሳልሰጥ በሥነ ፍጥረት ተመራምራችሁ አውቃችሁ
በሠራችሁት ብየ የምፈርድ ጽኑ ጨካኝ መሆኔን ታውቃለህን? እንዲህስ ካወቅህ ሹመትክን ልትመልስልኝ ይገባኝ ነበር፡፡
ወጥቶ ወርዶ ለሚያስተምር በሰጠሁት ነበር፡፡ አሁንም የእርሱን መምህርነት ሹመት ነሥታችሁ (ወስዳችሁ) ለዚያ
ደርቡለት! እርሱን ግን አውጡት የሚል ነው፡፡ ዛሬም እያንዳንዳችን በዓቅማችን መጠን መክሊት ተሰጥቶናል፡፡ በመሆኑም
መክሊቱን እንደቀበረው እንደዚያ ሰው የተሰጠንን ቀብረን ለወቀሳና ለፍርድ እንዳንሰጥ በአገልግሎታችን ልንተጋ
ይገባናል፡፡
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይህንኑ ሲገልጥ ‹‹አገልግሎት ቢሆን
በአገልግሎታችን እንትጋ የሚያስተምርም በማስተማሩ ይትጋ የሚሰጥም በልግሥና ይስጥ›› (ሮሜ12፥7) በማለት
ተናግሯል፡፡ ለመሆኑ ዛሬ ‹‹አንተ በጎ ታማኝ አገልጋይ…›› ተብሎ በእግዚአብሔር ሊመሰገን የሚችል ማን ይሆን?
በእውነት በዘመናችን እንዲህ ተብሎ የሚመሰገን በጎና ታማኝ ካህን’ ታማኝ መምህርና ሰባኪ’ ታማኝ ዘማሪ የመሳሰለውን
ማግኘት ይቻል ይሆንን? ትልቅ መሠረታዊ ሊሆን የሚገባው ጥያቄ ቢኖር ይህ ነው፡፡ ምክንያቱም ይህ የጌታችን
የኢየሱስ ክርስቶስ ትምህርት ስለ ታማኝነት የሁላችንንም ሕይወት የሚዳስስና ሁላችንንም የሚመለከት ነውና፡፡
በእርግጥም ዛሬም ቢሆን እንደ አባቶቻችን ማለትም እንደ ቅዱሳን
ሐዋርያት በእምነት’ በትዕግስት በፍቅር’ በትህትናና በትጋት በማገልገል የተሰጣቸውን መክሊት የሚያበዙ አገልጋዮች
አሉ፡፡ የእነዚህ ክብራቸው በምድርም በሰማይም እጅግ የበዛና ራሳቸውን አስመስለው በትምህርት የወለዷቸው ልጆቻቸውም
ለቤተክርስቲያን ውድ ልጆች ናቸው፡፡
ለምሳሌ ቅዱስ ጴጥሮስ ቀሌምንጦስን’ ቅዱስ ጳውሎስም ጢሞቴዎስን አፍርተዋል፡፡
ለምሳሌ ቅዱስ ጴጥሮስ ቀሌምንጦስን’ ቅዱስ ጳውሎስም ጢሞቴዎስን አፍርተዋል፡፡
ሌሎችም አበው ቅዱሳን በወንጌል ቃል መንፈሳውያንና ትጉሃን የሆኑ
ምእመናንን በሚገባ አፍርተዋል፡፡ ያላመኑትንም አሳምነው ወደ ቅድስት ቤተክርስቲያን በመመለስ ለዘላለማዊ ክብር
የበቁ እንዲሆኑ አስችለዋቸዋል፡፡ በመሆኑም በክርስቶስ በደሙ የተከፈለውን ወደር የሌለውን ዋጋ ዓለም አምኖና አውቆ
በክርስትና ሃይማኖት እንዲድንበትና እዲጠቀምበት በማድረግ እንዲሁም በታማኝነት ሥራቸው ጥንትም ዛሬም ላለችዋና
ወደፊትም ለምትኖርዋ ቅድስት ቤተክርስቲያን ድምቀትም ውበትም የሆኑት ቅዱሳን አበው ሊገኙ የቻሉት ከእግዚአብሔር
ይልቅ ሰውን ደስ ለማሰኘት በመድከማቸው ሳይሆን የተጠሩበትን ዓላማና የጠራቸውን እርሱን በሚገባ አውቀውና ከልብ
ተረድተው ለዘላለማዊ ህይወት ተግተው በመሥራታቸው ነው፡፡ (ገላ1፥10)
ዛሬም በዚህ ዘመን ያለንና በክርስቶስ ክርስቲያን ተብለን
የተጠራን ሁላችንም የተሰጠንን መክሊት (ጸጋ) አውቀን ለእግዚአብሔር ለአምላካችን በመታመን ወጥተን ወርደን ሌላ
ልናተርፍ ይገባናል፡፡ በተለይ ደግሞ በክህነት አገልግሎት ውስጥ ያለ ሰው ከምንም በላይ በከፍተኛ መንፈሳዊ ኃላፊነት
ላይ ያለ እንደመሆኑ መጠን በሃይማኖትም በሥነምግባርም ለሌላው ዓርዓያ በመሆን እንደ እርሱ ሃይማኖትን ከምግባር
ጋር አስተባብረው የያዙ ምእመናንን ማፍራት አለበት፡፡ ይህ ሲሆን ብቻ ነው አንተ በጎ ታማኝ ባሪያ በጥቂቱ
ታምነሃልና ወደ ጌታህ ደስታ ግባ ልንባል የምንችለው፡፡
አሁን ባለንበት በዘመናችን ብዙ ፈታኝ የሆኑ ችግሮች አሉ፡፡
የችግሮቹም መሠረታዊ ምንጭ በተጠሩበት ጸንቶ መቆም ፈጽሞ አለመቻልና ለሥጋዊ ጥቅም ብቻ በማድላት ኃላፊነትን
መዘንጋት ናቸው፡፡ በሥጋዊ አምሮት ፍላጎትና ምርጫ ውስጥ ደግሞ መንፈሳዊ ጸጋንና በረከትን ለማግኘት የሚያስችለንን
የታማኝነት ሥራን መሥራት አይቻልምና ከምናድነው ሰው ይልቅ መክሊታችንን በመቅበር መሰናክል የምንሆንበት ሰው ሊበዛ
እንደሚችል አያጠራጥርም፡፡ በመሆኑም ከእርሱ ዘንድ እንደዓቅማችን የተሰጠንን መንፈሳዊ ዕውቀት ለሌላው በማድረስ
መክሊታችንን ልናበዛ የምንችለውና አገልግሎታችን ወይም ክርስትናችን ውጤታማ የሚሆነው ምርጫችንን አውቀን እንደ ቃሉ
ሆነንና ጸንተን ስንገኝ ብቻ ነው፡፡
ይህ ባለመሆኑ ነው ዛሬ ብዙዎቻችን በህይወታችን ሌላውን ማትረፍ
አቅቶን በእግዚአብሔርና በሰውም ዘንድ በሚያስወቅሰን የስንፍና መንገድ ላይ ቆመን የምንገኘው፡፡ ስለዚህም ጌታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ ‹‹ ጌታችሁ በምን ሰዓት እንዲመጣ አታውቁምና እንግዲህ ንቁ›› (ማቴ24፥42) ብሎናል፡፡
እንግዲህ ቃሉን የሰማንና የምናውቅ ሁላችን በሞቱ ላዳነን፣
በልጅነት ጸጋም ላከበረን፣ በትንሣኤውም ላረጋጋን፣ በመስቀሉ ጥልን ገድሎ ከራሱ ጋር ላስታረቀን፣ በደሙም መፍሰስ
ህይወትን፣ ሰላምን፣ ፍቅርን፣ በረከትንና ዘላለማዊ ደስታን ለሰጠን አምላክ ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ
ክርስቶስ በመታመን እርሱ ያዘዘንን ሁሉ ልናደርግ ይገባናል፡፡ ምን ጊዜም ትጉህ ሠራተኛ ደግሞ የሚሠራው መልካም ሥራ
ሁሉ ለቤተ ክርስቲያንም ለሀገርም የሚሰጠው ጥቅም እጅግ ከፍተኛ ነው፡፡ በመሆኑም በጎና ታማኝ አገልጋዮች ሆነን
እንድንገኝ ጠንክረን ልንሠራ ይገባናል፡፡
የማይቀበሩ መክሊቶች
በዲ/ን ምትኩ አበራ
«ወደ ሌላ አገር የሚሔድ ሰው ባሮቹን ጠርቶ ያለውን ገንዘብ እንዲሰጣቸው እንዲሁ
ይሆናልና፣ ለእያንዳንዱ እንደአቅሙ ለአንዱ አምስት መክሊት ለአንዱ ሁለት ለአንዱም አንድ ሰጠና ወዲያው ሔደ…»
ማቴ 25÷14 ይህንን ታሪክ ማንሣታችን በወርኃ ዐቢይ ጾም በዕለተ ገብርሔር አንድም እየተባለ የሚተነተነውን ቃለ
እግዚአብሔር ለማውረድ ተፈልጎ አይደለም፡፡
ጌታችን የተናገራቸው ሁለቱ ኃይለ ቃላት የሚያስደምሙ ስለሆኑ ነው «… እንዲሁ ይሆናልና” የሚለውና
«ለእያንዳንዱ እንደአቅሙ» የሚሉት፡፡ ጌታችን እንዳለው እንዲሁ እንዳይሆንብን ዳሩ ግን እንዲሁ እንዲሆንልን ቅዱስ
ፈቃዱን እየተማፀን ለእያንዳንዳችን እንደአቅማችን የተሰጡንን የማይቀበሩ መክሊቶች በአጭሩ እንመልከት፡፡
እንደ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሥርዓትና እምነታችን እኛ በአርባና በሰማንያ ቀናችን በጥምቀት ከቅድስት
ቤተክርስቲያናችን የተወለድን ሁላችን፤ ባለጸጎች/የጸጋ ባለቤቶች፣ ነን « እንደተሰጠን ጸጋ ልዩ ልዩ ሥጦታ አለን»
ሮሜ 12÷6 ነገር ግን አንዳንዶች የተሰጠንን ጸጋ ባለማወቅ፣ ሌሎቻችንም የያዝነው ጸጋ ስጦታ ሳይሆን በእኛ ጥበብ
ያገኘነው እየመሰለን ወዘተ… እንኳንስ ልናተርፍባቸው ቀርቶ ቀብረናቸው፤ የጸጋውን ባለቤት «አንተ ካልዘራህበት
የምታጭድ፡፡ ካልበተንህበትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁና ፈራሁህ፣ ሔጄም መክሊትህን በምድር
ቀበርኩት እነሆ መክሊትህ» ለማለት የተዘጋጀን ይመስላል ማቴ 25÷24፡፡
እንድናተርፍባቸው ከተሰጡንና የማይቀበሩ ከሚባሉት መክሊቶቻችን መካከል ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸው፡፡
ዕውቀት እንድናተርፍባቸው ከተሰጡንና የማይቀበሩ ከሚባሉት መክሊቶቻችን መካከል ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸው፡፡
ዕውቀት ለፍጡራን ሁሉ የባሕርይ ሳይሆን ተከፍሎ የሚሰጥና የሚነሳ /የሚወሰድ/ ነው፡፡ ይህ ዕውቀት
መክሊት/ስጦታ/ ነው፤ 1ቆሮ21÷7 የተሰጠበት ምክንያት ደግሞ እንድንታበይበት ሳይሆን ለሌላው እንድንጠቅምበት
ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ «ዕውቀት ያስታብያል» ስለሚል አበው ሲመርቁ ዕውቀት ያለትዕቢት ይስጥህ፤ ይላሉ
1ቆሮ1-3፡፡ ዲያብሎስ አዋቂ ተደርጐ ተፈጥሯልና አዋቂ ነው፡፡ በዚህ ዕውቀቱ ግን እሱ ጠፍቶበት ሌላውን ለማጥፋት
ይተጋበታል እንጅ ለሌላው ለመጥቀም አንዳች አይሠራም፡፡ ሰው በተሰጠው ዕውቀቱ በጎ ሥራን እንዲሠራበትና ለሌላው
እንዲተርፍበት እግዚአብሔር ይሻል፡፡ እግዚአብሔር የሚጠይቀን በተሰጠን የዕውቀት መክሊት ክፉ ሥራ ስለሠራንበት ብቻ
አይደለም በዕውቀታችን መጠን ያላወቀውን ከማሳወቅ ጀምሮ ምን ያህል እንደሠራንበት ይመረምረናል፡፡ ስለዚህ ብዙ
ባወቅን ቁጥር ብዙ ማትረፍ እንዳለብን መረዳት ያሻል፡፡ «ብዙ ከተሰጠው ሰው ሁሉ ከእርሱ ብዙ ይፈለግበታል»
ተብሏልና፡፡
ሀብት
በመጀመሪያ ደረጃ ሀብታም/ባለሀብት/ መሆን በክርስትና ሕይወት አይነቀፍም፡፡ ለእግዚአብሔር ፍርድ ምድራዊ ሀብት መመዘኛ አይሆንም፡፡ እሱ ሀብታሙን ፈርቶ ድሃውን ንቆ ሳይሆን ለሁሉም እንደየሥራቸው ነው የሚፈርድባቸው፤ ራዕ 22÷12 ሀብት በምንለው በዚህ ዓለም በንብረትና ገንዘብ በከበርን ጊዜ ሁላችን ልናስታውሰው የሚገባ ቁምነገር አለ፡፡
• አንደኛ የሰጠን እግዚአብሔር መሆኑን መዘንጋት የለብንም፡፡ እርግጥ ነው ወጥተን ወርደን ጥረን ግረን ሥራ ሳንመርጥ በላባችን ወዝ ያፈራነው የድካማችን ውጤት ነው፡፡ ግን ይህን ሁሉ ብቻችንን ልናደርገው አንችልም፡፡ በመግባት በመውጣታችን ጊዜ የረዳን፣ ጉልበታችንን ያጠነከረ፣ እጃችንን ያበረታ፣ ጤናውን የሰጠን እግዚአብሔር ነው፡፡ ለዚህ ነው ቅዱስ መጽሐፍ «ጉልበቴ የእጄም ብርታት ይህን ሀብት አመጣልኝ እንዳትል» የሚለን /ዘዳ 8÷17/፡፡
• ሁለተኛው ደግሞ ታማኝ መጋቢ እንድንሆንለት ማለትም ቀን ከፍቶበት ሆድ ብሶት ሲቸገር ያየነውን ወንድማችንን ችግሩን እንድናስወግድለት ላጣውና ለነጣው ድሃ እንድንደርስለት ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለመንፈስ ቅዱስ ልጁ ለጢሞቴዎስ «ባለጠጎች ሊረዱና ሊያካፍሉ የተዘጋጁ እንዲሆኑ ምከራቸው» ያለው፤ ይህንኑ ለማስታወስ ነው 1ኛ ጢሞ 6÷19 ጠቢቡ ሰሎሞንም ሀብት የማትረፊያ መክሊት መሆኑን ሲያስረዳ «ያለውን የሚበትን ሰው አለ፤ ይጨመርለታልም፤ ያለቅጥ የሚነፍግ ሰውም አለ ይደኸያልም» ነው ያለው ምሳ 11÷24 ይህ ሰው ለሰዎች ሲሰጥ በምድር ይከፍሉኛል ብሎ አስቦ ባለመሆኑ የሚበትን በማለት በዚህ በሚያልፈው ምድራዊ ሀብት የማያልፈውን ሰማያዊ ሀብት ማትረፍ እንዲቻል የነገረንን ልብ እንበል፡፡ ቀላል ምሳሌ እናስቀምጥ፤ በሰፈራችን አንድ ትልቅ ድግስ ላይ የድግሱ ባለቤት ጐረቤቶቹንና ወዳጆቹን ጠርቶ፤ የድግሱ እድምተኞች ከመምጣታቸው አስቀድሞ፤ አንዱን ወጥቤት፣ ሌላውን ሥጋ ቤት፣ ሌላዋን እንጀራ ቤት ወዘተ እያለ ይመድባል፡፡ እነዚህ ሰዎች የድግስ ቤቱ ሹማምንት ቢሆኑም ድግሱ የእነሱ አይደለም ስለዚህ በሰው ድግስ ለመጠቃቀም አንዱ ባዶ ሳህን ይዞ እያዩ ለሌላው ሁለተኛ እንጀራ ቢደርቡለት፣ አንዱ ደረቅ እንጀራ እየበላ ለሚያውቁት የሰፈራቸው ሰው የወጥ ሳህኑን አቅርበው ወጡን ቢገለብጡለት፣ የሰው ድግስ በማበላሸታቸው ይጠየቁበታል እንጂ አይመሰገኑበትም የዚህ ዓለም ባለጸጐችም እንዲሁ ናቸው የተሰጣቸው ሀብት ሊያጋፍሩበት፣ ሊያስተናብሩበት፣ መክሊት ሊያተርፉበት እንጂ በዚህ ዓለም ሊመራረጡበት በልጠው ሊታዩበት ወዘተ… አይደለም፡፡ « የአመጻ ገንዘብ ሲያልቅ በዘላለም ቤቶች እንዲቀበሏችሁ በእርሱ ወዳጆችን ለራሳችሁ አድርጉ” የተባለውን፤ ባለጸጎች ሁሉ ልብ ሊሉት ይገባል፡፡/ሉቃ 16÷9/
ሥልጣን
ሌላኛው መክሊት ሥልጣን ነው፡፡ ሥልጣን ሲባል ሁሌም ትዝ የሚለን ያየነውም እሱኑ ብቻ ስለሆነ ይመስላል፤ መፍለጥ መቁረጥ፣ ማራድና ማንቀጥቀጥ ነው፡፡ ተረታችንም «ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል» የሚል ነው፡፡ በዚህ መንፈስ ብዙዎች «እኔ እግዚአብሔርን ብሆን ኖሮ…» ብለው የሚፎክሩት አይሆኑም እንጂ ቢሆኑ ኖሮ፤ ከቤተ ክርስቲያን የሚያባርሩት፣ ከሥልጣን የሚሽሩት ወደሞት የሚያወርዱት ባጠቃላይ የሚፈልጡትና የሚቆርጡት ብዙ ነው፡፡ አላወቁትም እንጂ እግዚአብሔርን መሆን እነሱ እንዳሰቡት መቅሰፍ መግደል ብቻ ሳይሆን፤ እግር ማጠብ በጥፊ መመታት፣ በምራቅ መታጠብ፣ የእሾህ አክሊል መድፋት፣ በጦር መወጋት፣ ለሰው ልጆች ድኀነት መሰቀልና መሞትም ነው፡፡ በአንጻሩ በተሰጠው መክሊት ያላተረፈው፤ ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል በሚል አሳብ ተተብትቦ፤ ሥልጣን መፍለጥ መቁረጥ የመሠለው ምስኪን የሚያገኘውን ዕድል በምሳሌ ሲያስረዳ እንዲህ ብሏል፡፡ «ያባሪያ ግን ጌታዬ እስኪመጣ ይዘገያል ብሎ በልቡ ቢያስብ ሎሌዎችንና ገረዶችንም ይመታ፣ ይበላም ይጠጣም ይሰክርም ዘንድ ቢጀምር የዚያ ባሪያ ጌታ ባልጠበቃት ሰዓት ይመጣል ከሁለትም ይሰነጥቀዋል ዕድሉንም ከማይታመኑ ጋር ያደርጋል፡፡» /ሉቃ 12÷42-46/፡፡ ጥሩ ክርስቲያን ባለሥልጣን ሲሆን አይኮፈስም፤ «ጌታው በቤተሰቦቹ ላይ የሾመው፡፡» ተብሎ እንደተጠቀሰው፤ በእግዚአብሔር ፍጥረት ላይ በመሾሙ እንደጠቢቡ ሰሎሞን ይህንን ሕዝብ የማስተዳድርበት ጥበብ ስጠኝ እያለ ወደ ፊጣሪው በመጸለይ መክሊቱን ለማትረፍ ይተጋል፡፡
አንድ ታሪክ እናስታውሳችሁ፤ የሊቀ ጳጳሱ የዲሜጥሮስን ወደ ጵጵስና መዓርግ መምጣት እናቱ ሰምታ «ሹ
ሀብት
በመጀመሪያ ደረጃ ሀብታም/ባለሀብት/ መሆን በክርስትና ሕይወት አይነቀፍም፡፡ ለእግዚአብሔር ፍርድ ምድራዊ ሀብት መመዘኛ አይሆንም፡፡ እሱ ሀብታሙን ፈርቶ ድሃውን ንቆ ሳይሆን ለሁሉም እንደየሥራቸው ነው የሚፈርድባቸው፤ ራዕ 22÷12 ሀብት በምንለው በዚህ ዓለም በንብረትና ገንዘብ በከበርን ጊዜ ሁላችን ልናስታውሰው የሚገባ ቁምነገር አለ፡፡
• አንደኛ የሰጠን እግዚአብሔር መሆኑን መዘንጋት የለብንም፡፡ እርግጥ ነው ወጥተን ወርደን ጥረን ግረን ሥራ ሳንመርጥ በላባችን ወዝ ያፈራነው የድካማችን ውጤት ነው፡፡ ግን ይህን ሁሉ ብቻችንን ልናደርገው አንችልም፡፡ በመግባት በመውጣታችን ጊዜ የረዳን፣ ጉልበታችንን ያጠነከረ፣ እጃችንን ያበረታ፣ ጤናውን የሰጠን እግዚአብሔር ነው፡፡ ለዚህ ነው ቅዱስ መጽሐፍ «ጉልበቴ የእጄም ብርታት ይህን ሀብት አመጣልኝ እንዳትል» የሚለን /ዘዳ 8÷17/፡፡
• ሁለተኛው ደግሞ ታማኝ መጋቢ እንድንሆንለት ማለትም ቀን ከፍቶበት ሆድ ብሶት ሲቸገር ያየነውን ወንድማችንን ችግሩን እንድናስወግድለት ላጣውና ለነጣው ድሃ እንድንደርስለት ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለመንፈስ ቅዱስ ልጁ ለጢሞቴዎስ «ባለጠጎች ሊረዱና ሊያካፍሉ የተዘጋጁ እንዲሆኑ ምከራቸው» ያለው፤ ይህንኑ ለማስታወስ ነው 1ኛ ጢሞ 6÷19 ጠቢቡ ሰሎሞንም ሀብት የማትረፊያ መክሊት መሆኑን ሲያስረዳ «ያለውን የሚበትን ሰው አለ፤ ይጨመርለታልም፤ ያለቅጥ የሚነፍግ ሰውም አለ ይደኸያልም» ነው ያለው ምሳ 11÷24 ይህ ሰው ለሰዎች ሲሰጥ በምድር ይከፍሉኛል ብሎ አስቦ ባለመሆኑ የሚበትን በማለት በዚህ በሚያልፈው ምድራዊ ሀብት የማያልፈውን ሰማያዊ ሀብት ማትረፍ እንዲቻል የነገረንን ልብ እንበል፡፡ ቀላል ምሳሌ እናስቀምጥ፤ በሰፈራችን አንድ ትልቅ ድግስ ላይ የድግሱ ባለቤት ጐረቤቶቹንና ወዳጆቹን ጠርቶ፤ የድግሱ እድምተኞች ከመምጣታቸው አስቀድሞ፤ አንዱን ወጥቤት፣ ሌላውን ሥጋ ቤት፣ ሌላዋን እንጀራ ቤት ወዘተ እያለ ይመድባል፡፡ እነዚህ ሰዎች የድግስ ቤቱ ሹማምንት ቢሆኑም ድግሱ የእነሱ አይደለም ስለዚህ በሰው ድግስ ለመጠቃቀም አንዱ ባዶ ሳህን ይዞ እያዩ ለሌላው ሁለተኛ እንጀራ ቢደርቡለት፣ አንዱ ደረቅ እንጀራ እየበላ ለሚያውቁት የሰፈራቸው ሰው የወጥ ሳህኑን አቅርበው ወጡን ቢገለብጡለት፣ የሰው ድግስ በማበላሸታቸው ይጠየቁበታል እንጂ አይመሰገኑበትም የዚህ ዓለም ባለጸጐችም እንዲሁ ናቸው የተሰጣቸው ሀብት ሊያጋፍሩበት፣ ሊያስተናብሩበት፣ መክሊት ሊያተርፉበት እንጂ በዚህ ዓለም ሊመራረጡበት በልጠው ሊታዩበት ወዘተ… አይደለም፡፡ « የአመጻ ገንዘብ ሲያልቅ በዘላለም ቤቶች እንዲቀበሏችሁ በእርሱ ወዳጆችን ለራሳችሁ አድርጉ” የተባለውን፤ ባለጸጎች ሁሉ ልብ ሊሉት ይገባል፡፡/ሉቃ 16÷9/
ሥልጣን
ሌላኛው መክሊት ሥልጣን ነው፡፡ ሥልጣን ሲባል ሁሌም ትዝ የሚለን ያየነውም እሱኑ ብቻ ስለሆነ ይመስላል፤ መፍለጥ መቁረጥ፣ ማራድና ማንቀጥቀጥ ነው፡፡ ተረታችንም «ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል» የሚል ነው፡፡ በዚህ መንፈስ ብዙዎች «እኔ እግዚአብሔርን ብሆን ኖሮ…» ብለው የሚፎክሩት አይሆኑም እንጂ ቢሆኑ ኖሮ፤ ከቤተ ክርስቲያን የሚያባርሩት፣ ከሥልጣን የሚሽሩት ወደሞት የሚያወርዱት ባጠቃላይ የሚፈልጡትና የሚቆርጡት ብዙ ነው፡፡ አላወቁትም እንጂ እግዚአብሔርን መሆን እነሱ እንዳሰቡት መቅሰፍ መግደል ብቻ ሳይሆን፤ እግር ማጠብ በጥፊ መመታት፣ በምራቅ መታጠብ፣ የእሾህ አክሊል መድፋት፣ በጦር መወጋት፣ ለሰው ልጆች ድኀነት መሰቀልና መሞትም ነው፡፡ በአንጻሩ በተሰጠው መክሊት ያላተረፈው፤ ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል በሚል አሳብ ተተብትቦ፤ ሥልጣን መፍለጥ መቁረጥ የመሠለው ምስኪን የሚያገኘውን ዕድል በምሳሌ ሲያስረዳ እንዲህ ብሏል፡፡ «ያባሪያ ግን ጌታዬ እስኪመጣ ይዘገያል ብሎ በልቡ ቢያስብ ሎሌዎችንና ገረዶችንም ይመታ፣ ይበላም ይጠጣም ይሰክርም ዘንድ ቢጀምር የዚያ ባሪያ ጌታ ባልጠበቃት ሰዓት ይመጣል ከሁለትም ይሰነጥቀዋል ዕድሉንም ከማይታመኑ ጋር ያደርጋል፡፡» /ሉቃ 12÷42-46/፡፡ ጥሩ ክርስቲያን ባለሥልጣን ሲሆን አይኮፈስም፤ «ጌታው በቤተሰቦቹ ላይ የሾመው፡፡» ተብሎ እንደተጠቀሰው፤ በእግዚአብሔር ፍጥረት ላይ በመሾሙ እንደጠቢቡ ሰሎሞን ይህንን ሕዝብ የማስተዳድርበት ጥበብ ስጠኝ እያለ ወደ ፊጣሪው በመጸለይ መክሊቱን ለማትረፍ ይተጋል፡፡
አንድ ታሪክ እናስታውሳችሁ፤ የሊቀ ጳጳሱ የዲሜጥሮስን ወደ ጵጵስና መዓርግ መምጣት እናቱ ሰምታ «ሹ